<?xml version="1.0" encoding="UTF-8"?>
<rss  version="2.0">
    <channel>
        <title>WALTA INFORMATION CENTER, AMHARIC NEWS</title>
        <description>Walta Information Center is a private news and information service establishment based in Addis Ababa , Ethiopia.&lt;br&gt;</description>
        <link>http://www.waltainfo.com</link>
        <category>AMHARIC</category>
        <copyright>Copyright ECTV</copyright>
        <docs>http://blogs.law.harvard.edu/tech/rss</docs>
        <language>en</language>
        <lastBuildDate>Fri, 13 Jun 2008 11:38:16 -0400</lastBuildDate>
        <managingEditor>webmaster@ectv.org</managingEditor>
        <pubDate>Fri, 13 Jun 2008 11:34:19 -0400</pubDate>
        <webMaster>webmaster@ectv.org</webMaster>
        <generator>FeedForAll Mac v2.1 (2.1.0.1); http://www.FeedForAll.com/</generator>
        <image>
            <url>http://www.waltainfo.com/Resource/walta2.gif</url>
            <title>Walta Information Center</title>
            <link>http://www.waltainfo.com/</link>
            <description>Walta Information Center, Addis Ababa, Ethiopia</description>
            <width>120</width>
            <height>70</height>
        </image>
        <item>
            <title>የምግብ እህል እጥረቱና የተጎጂዎችን ቁጥር አጋነው የሚያቀርቡ ወገኖች ኢኮኖሚያዊ እድገቱን ለማጣጣል የሚፈልጉ መሆናቸው ተገለፀ</title>
            <description><![CDATA[አዲስ አበባ ሰኔ 5/2000/ዋኢማ/ በኢትዮጵያ ያጋጠመውን የምግብ እህል እጥረትና የተጎጂዎችን ቁጥር አጋነው የሚያቀርቡ ወገኖች በአገሪቱ እየተመዘገበ ያለውን ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ለማጣጣል የሚፈልጉና በጉዳዩ የራሳቸውን ጥቅም አብረው የሚያሰሉ መሆናቸውን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የግብርናና ገጠር ልማት ሚኒስትር አስታወቁ።<br />
ሚኒስትሩ አቶ አዲሱ ለገሰ ዛሬ በጽህፈት ቤታቸው በሰጡት መግለጫ እንዳስታወቁት፤ አንዳንድ በአስቸኳይ እርዳታ ላይ የተመሰረተ ተግባር የሚያከናውኑ ወገኖች የተረጂዎች ቁጥር መቀነስን በህልውናቸው ላይ የመጣ አደጋ አድርገው እንደሚቆጥሩት ጠቅሰው፤ ብዙ እርዳታ እንዲገኝ ቁጥሩን በርከት አድርገን እናቅርብ የሚል ሃሳብ ሲያቀርቡ መቆየታቸውን ገልፀዋል።<br />
 <br />
ከበልግ ዝናብ ዕጥረት ጋር በተያያዘ በተወሰኑ በልግ አብቃይ አካባቢዎች የምግብ እህል እጥረት ያጋጠማቸው ዜጎች ቁጥር 4 ነጥብ 6 ሚሊየን መሆኑን አቶ አዲሱ አስታውቀው፣ መንግስት ለተረጂዎች ተገቢውን ድጋፍ እያደረገ መሆኑንና የተረጂዎችን ቁጥር በተመለከተ በአንዳንድ ወገኖች የሚቀርበው አሃዝ እጅግ የተጋነነ እንደሆነ ገልጸዋል።<br />
 <br />
የተጎጂዎችን ቁጥር በተመለከተ የተዛቡና ወጥነት የሌላቸው አሀዞች በተለያዩ ወገኖች ሲቀርቡ የቆዩ ቢሆንም መንግስት ችግሩ በተከሰተባቸው አካባቢዎች ባደረገው ጥናት የምግብ እህል እጥረት ያጋጠማቸው ዜጎች ቁጥር 4 ሚሊየን 617 ሺ 300 መሆኑ ተረጋግጧል።<br />
 <br />
መንግስት በጉዳዩ ላይ ተገቢው ጥናት ከተካሄደ በኋላ ትክክለኛውን አሃዝ የመግለጽ አማራጭን መከተሉን የገለጹት አቶ አዲሱ፤ ይህን ያደረገውም በዓለም አደባባይ በልመና ተወዳዳሪ መሆን የሚያኮራ ድርጊት አለመሆኑን በመገንዘብ እንደሆነ አቶ አዲሱ አመልክተዋል።<br />
 <br />
በሴፍትኔት የታቀፉ ወገኖችን ጭምር እንደሚያካትት የገለጹት አቶ አዲሱ፤ ከዚህ ውስጥ ክትትልና ድጋፍ የሚፈልጉት ከአምስት ዓመት በታች ያሉ ህጻናት ቁጥር 75 ሺ ብቻ መሆኑን ጠቁመዋል።<br />
 <br />
መንግስት በእርዳታ ሰጪ ድርጅቶች የቀረቡ በግምት ላይ የተመሰረቱና የተጋነኑ መረጃዎች በጥናት እንዲረጋገጡ ማድረጉንና ከጥናቱ ጎን ለጎንም ለተጎጂ ወገኖች እርዳታ ማቅረቡን ገልጸው፤ የምግብ እህል እጥረቱ በደቡብ ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች፣ በኦሮሚያ፣ በሶማሌ፣ በአማራና ትግራይ ክልሎች በሚገኙ አንዳንድ ወረዳዎች ማጋጠሙን ተናግረዋል።<br />
 <br />
ተጎጂዎች ያጋጠማቸውን ችግር ለማቃለል በተደረገ ጥረት ካለፈው የካቲት ጀምሮ ከ775 ሺ ኩንታል የሚበልጥ እህል ለተጎጂዎች መከፋፈሉን ጠቁመው፤ 50 ሚሊየን ብር በጀት በመመደብ የህክምና አገልግሎት መሰጠቱን ገልጸዋል።<br />
 <br />
በአካባቢዎቹ ያጋጠመውን የውሃ እጥረት ለማቃለል የነባር ጉድጓዶችን ጥልቀት በመጨመርና በቦቴ በማመላለስ ጥረት መደረጉን ያመለከቱት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ በአርብቶ አደር አካባቢዎች ለእንስሳት መኖ የማቅረብና ለአርቢዎች ገበያ የማፈላለግ ድጋፍ መደረጉን ገልጸዋል ።<br />
 <br />
መንግስት ከደጋፊዎቹ ጋር በመሆን እያደረገ ያለውን የምግብ እህልና አልሚ ምግብ የማቅረብ ተግባር አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸው፤ ባለፈው ግንቦት ወር የተገኘውን ዝናብ በመጠቀምም ቶሎ ሊደርሱ የሚችሉ ሰብሎችን በመዝራት የማካካስ ስራ እየተሰራ መሆኑን መናገራቸውን ዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል ዘግቧል።]]></description>
            <link>http://www.waltainfo.com/index.php?option=com_content&amp;task=view&amp;id=446&amp;Itemid=44</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">F06227BD-395D-11DD-A833-000393197FB0-4056-0000005597690169-FFA</guid>
            <pubDate>Fri, 13 Jun 2008 11:34:28 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ከስኬታማ ሰዎች የሚያገኙት ተመክሮ ጠቃሚ መሆኑ ተገለፀ</title>
            <description><![CDATA[አዲስ አበባ ሰኔ 5/2000 ዋኢማ/የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች በትምህርት ገበታ ከሚያገኙት የቀለም ትምህርት በተጨማሪ በተለያዩ መስኮች ከተሰማሩ ባለሙያዎች የሚያገኙት ተመክሮ ወደ ስራ አለም ሲሸጋገሩ እንደሚያግዛቸው ክቡር ዶክተር አትሌት ሻለቃ ኃይሌ ገብረስላሴ ገለፀ።<br />
 <br />
 <br />
አትሌት ሻለቃ ኃይሌ ትናንት በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ቴክኖሎጂ ፋኩልቲ አዳራሽ ስለሙያው ስኬትና ተያያዥነት ባላቸው ጉዳዮች ላይ ከተማሪዎች ጋር ውይይት ባደረገበት ወቅት አንደገለፀው፤ ተማሪዎች በዩኒቨርስቲው ያገኙትን ትምህርት ተከታትለው ተመርቀው ከወጡ በኋላ በሚገባ መተግበር የሚያስችሉ ተሞክሮዎችን ማግኘት አለባቸው።<br />
 <br />
ተማሪዎቹም ሆኑ መምህራኑ የቆሙለትን ዓላማ ለማሳካት ጠንክረው በመስራት ለውጤት መብቃት እንደሚችሉ የገለፀው አትሌት ኃይሌ ፅናትን ተላበሶ የሰራ ሰው ስኬታማ መሆኑ አያጠራጥርም ብሏል።<br />
 <br />
አገራችን በአሁኑ ወቅት በሰፊ የልማትና የእድገት እንቅስቃሴ ላይ በመሆኗ የተማሩ ኃይሎች ይህንን ልማት የበለጠ ለማጎልበት ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ መስራት እንደሚጠበቅባቸው አስረድቷል።<br />
 <br />
ሩጫ ሲጀምር በተሳተፈበት ውድድር 99ኛ የወጣበት ወቅት እንደነበረና በወቅቱ አባቱን ጨምሮ ሌሎች ወዳጆቹ ሩጫ ጠቀሜታ እንደሌለው ቢገልፁለትም በእልህና ተስፋ ባለመቁረጥ ባደረገው ጥረት ከ25 በላይ ሪከርዶችን ሊያስመዘግብ መቻሉንና ሰው ከጣረ ካቀደው በላይ መሄድ ይችላል ብሏል።<br />
 <br />
በቢዝነሱም በኩል ጤናማ የሆነ ልማትና ዕድገት ለማመጣት የሚያስችሉ ስልቶችን በመከተል እየሰራ እንደሆነና አሁን ያለውን ስኬት የበለጠ በመስራት ለማሳደግ ቀን ከሌት እየሰራ መሆኑን አትሌት ሻለቃ ኃይሌ ተናግሯል።<br />
 <br />
በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የኢንደስትሪ ፓርትነርሽፕ ፕሮግራም ዳይሬክተር ዶክተር ኢንጀነር ዳንኤል ቅጣው በዚህ ወቅት እንደገለጹት፤ ይህ አይነቱ መድረክ በተለያዩ የሙያ ስምሪቶች የተሳካላቸውን ሰዎች በመጋበዝ የተማሪዎችን ግንዛቤ ማሰፋትና የህይወት መርሆችን እንዲረዱ ማድረግን አላማ ያደረገ ነው ብለዋል።<br />
 <br />
በቀጣይም ሰፊ ተሞክሮ ያላቸውንና በለይም በቢዝነስ፣ በኮንስትራክሽንና በተዛማች ዘርፎች ላይ በማተኮር ባለሙያዎችን በመጋበዝ እንደሚያወያዩም ዳይሬክተሩ ገልፀዋል።<br />
 <br />
አትሌት ሻለቃ ኃይሌ ገብረስላሴ ለቴክኖሎጂ ፋኩልቲ ተማሪዎች የትምህርት አገልግሎት የሚውል ከ400 የሚበልጥ የራየቲንግ ፓድ በስጦታ ለተማሪዎች አከፋፍሏል።<br />
 <br />
በዩኒቨርስቲው የመካኒካል ኢንጅነሪንግ የመጀመሪያ ዲግሪ፤ የድህረ ምረቃ፤ የፒኤችዲ እጩ ተመራቂዎችና መምህራንን ጨምሮ ከ500 በላይ ተሳታፊዎች ኃይሌ በስፖርቱና በቢዝነስ ላይ ያገኘውን ስኬት አስመልክተው የግማሽ ቀን ውይይት ማድረጋቸውን ዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል ዘገቧል።]]></description>
            <link>http://www.waltainfo.com/index.php?option=com_content&amp;task=view&amp;id=434&amp;Itemid=44</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">D415A07C-395C-11DD-A833-000393197FB0-4056-00000051E716C88C-FFA</guid>
            <pubDate>Fri, 13 Jun 2008 11:32:31 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>የኤርትራ መገናኛ ብዙኋን የጎረቤት አገሮች ሰላምን በማደፍረስ ተግባር ላይ መጠመዳቸው ተገለጸ</title>
            <description><![CDATA[መቀሌ ግንቦት 10/2000/ዋኢማ/ የኤርትራ መገናኛ ብዙኋን የአገሪቱን አንገብጋቢ የሰላም፤የዴሞክራሲና የልማት ጉዳዮች ላይ ከማትኮር ይልቅ በጎረቤት አገሮች ሰላም ማደፍረስ ተግባር ላይ መጠመዳቸው አሳፋሪ ተግባር መሆኑን ሰሞኑን ወደ ኢትዮጵያ የገባ ኤርትራዊ ጋዜጠኛ አስታወቀ ።<br />
<br />
የኤርትራ መንግሥት የግፍ አገዛዝን በመቃወም ሰሞኑን ወደ ኢትዮጵያ የገባው በኤርትራ ቴሌቪዥንና ሬድዮ ይሰራ የነበረው ጋዜጠኛ ገብረመድህን አብረሃ እንደገለጸው፤የኤርትራ ህዝብ በሻዕቢያ የሚደርስበት ስቃይና መከራ በአሁኑ ወቅት አስከፊ ደረጃ ላይ ደርሷል ።<br />
<br />
የሻዕቢያ መንግስት የሚቆጣጠራቸው የኤርትራ መገናኛ ብዙኋን የአገሪቱን አንገብጋቢ ጥያቄዎች የሆኑ የሰላም፤የዴሞክራሲና የልማት ጉዳዮች ላይ ከማትኮር ይልቅ ዋነኛ አጀንዳቸውና ጊዚያቸው በጎሮቤት አገሮች አልቧልታ ላይ መጠመዳቸውን አመልክቷል ።<br />
<br />
የኤርትራ ህዝብ ህልውና ከባድ ፈተና ውስጥ በወደቀበት በአሁኑ ወቅት የኢሳያስ መንግስት የኤርትራ ሃብትና ንብረትን የጎሮቤት አገሮች የውስጥ ጉዳይን ለማተራመስና ተቃዋሚ ድርጅቶች ለመደገፍ እያዋለው እንደሚገኝ ገልጾ የኤርትራ ህዝብ ስለራሱ የውስጥ ጉዳይ የሚመክርበት የሰላም አየር ለማምጣት ሻዕቢያን በቃህ ሊለው ይገባል ብሏል።<br />
<br />
ኤርትራ ዜጎቿ የመናገርና የማሰብ መብታቸው አጥተው የሲኦል ኑሮ እንዲገፉ ተገደዋል ያለው ጋዜጠኛ ገብረመድህን በስርዓቱ የተማረሩ ወጣቶች ህይወታቸውን ለማቆየት ወደ ተለያዩ አገሮች መሰደድ ብቸኛው አማራጭ እየሆነ መምጣቱን ገልጿል።<br />
<br />
ብዙሃን ኤርትራውያን ከፖለቲካዊ ስልጣንና ከልማቱ ተገልለው የኢሳያስን አገዛዝ አሜን ብለው እንዲቀበሉ በመሳሪያ ሃይል በታፈኑበት በአሁኑ ወቅት ጥቂት ባለሥልጣናትና ወታደራዊ አዛዦች እንዳሻቸው የሚፈነጩባት አገር እንደሆነች መታዘቡን ገልጿል።<br />
<br />
አገሪቱን ለመምራት ህጋዊ መሰረትም ሆነ ተጠያቂነት የሌለው የኢሳያስ መንግሥት ኤርትራን እንደአገር ለጥፋት እየዳረጋት በሚገኝበትና የተለየ አመለካከት የያዙ ዜጎቿ በሚታሰሩባትና በሚገደሉባት በአሁኑ ወቅት የኤርትራ መገናኛ ብዙኋን ኤርትራ ወንጀል የማይፈጸምባት ብቸኛ አገር ነች የሚል መዝሙር መስማት የተለመደ ቅጥፈት መሆኑን አብራርቷል።<br />
<br />
የኤርትራ ህዝብ ካሁን ወዲያ የሻዕቢያን የግፍ አገዛዝ ተሸክሞ የሚያዘግምበት ወቅት እያከተመ መሆኑን የተናገረው ጋዜጠኛ ገብረመድህን ሁሉም ዜጋ ለኤርትራ ህዝብና ለአካባቢው ሰላም ጠንቅ የሆነውን ስርዓት ለመጣል መነሳሳት እንዳለበት ጥሪ ማቅረቡን ዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል ዘግቧል።]]></description>
            <link>http://www.waltainfo.com/AmNews/2008/May/18May08/46933.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">AFCA46DB-2597-11DD-B3D6-000393197FB0-3776-0000003A60D7BCF8-FFA</guid>
            <pubDate>Mon, 19 May 2008 07:36:09 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>የኢትዮ ሱዳንን ድንበር በተመለከተ ሚዲያዎች ያስተላለፉት ዘገባ ከዕውነት የራቀ መሆኑ ተገለፀ</title>
            <description><![CDATA[አዲስ አበባ ግንቦት 7/2000/ዋኢማ/የኢትዮ ሱዳንን ድንበር በተመለከተ የተለያዩ የውጭ የዜና ማሰራጫዎችና የግል ሚዲያዎች ያስተላለፉት ዘገባ ከዕውነት የራቀና የሁለቱን ሀገራት ሰላም ለማናጋት የተቀነባበረ መሆኑን የቤኒሻንጉል ክልል ርዕሰ መስተዳደር አቶ ያረጋል አይሸሹም አስታወቁ።<br>
<br>
ርዕሰ መስተዳድሩ አቶ ያረጋል አይሸሹም ዛሬ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ላይ እንዳስታወቁት፤ሁለቱ ሀገራት በሚዋሰኑበት ድንበር አካባቢ እስካሁን ምንም አይነት ችግር ሳይከሰት ተባብረውና ተደጋግፈው እየኖሩ ነው።<br>
<br>
የአሜሪካና የጀርመን ድምጽ ሬድዮ አገልገሎቶችና ሌሎች ሚዲያዎች ኢትዮጵያ ለሱዳን መሬት ቆርሳ ሸጣለች በማለት ሰሞኑን የሚያናፍሱት ወሬ የሁለቱን አገሮች ሰላም ለማደናቀፍ ካልሆነ በስቀር እውነትነት እንደሌለው አስረድተዋል።<br>
<br>
የድንበር ጉዳይን በተመለከተ የድንበር ማካለል ኮሚሽኑ ከተለያዩ አካላት ጋር በመሆን ጥናት ከመጀመሩ በስተቀር ወደ ድንበር ማካለል ገና አለመግባቱን ያስታወቁት አቶ ያረጋል፤ ድንበሩ ተካሎ እንዳለቀና ከኢትዮጵያ ተቆርጦ ለሱዳን እንደተሰጠ ተደርጎ በዜና ማሰራጫዎች መቅረቡ የሙያ ስነ ምግባርን የሚጥስና የሁለቱን ሀገራት ህዝቦች ወደ አላስፈላጊ ብጥብጥ እንዲገቡ የሚጋብዝ ነው ብለዋል።<br>
<br>
የሁለቱ ሀገሮች ህዝቦች በአሁኑ ወቅት ከድህነት ለመውጣት ሰፊ እንቅስቃሴ እያደረጉና በድንበር አካባቢ ያለው ህብረተሰብ በሰላም ኑሮውን እየገፋ እንደሚገኝ ጠቁመው፤ የሚነዛውን ወሬ ወደጎን በመተው የጀመረውን ልማት አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ተናግረዋል።<br>
<br>
የድንበር ማካለል ሂደቱ ዓለም አቀፍ መርህን በተከተለና ፍጹም ሰላም በሰፈነበት ሁኔታ የሚካሄድ መሆኑን ያረጋገጡት አቶ ያረጋል፤ጠባብ የፖለቲካ ድርጅቶችና የእነሱን ወሬ የሚያናፍሱ ሚዲያዎች ከድርጊታቸው ሊቆጠቡ እንደሚገባ አሳስበዋል።<br>
<br>
በተመሳሳይ በቤኒሻንጉል ክልል ጠረፋማ አካባቢዎች ሻዕቢያና የሻዕቢያ ቅጥረኞች ከሚያዚያ ወር ጀምሮ በክልሉ በተለያዩ ጠረፋማ አካባቢዎች የህዝቡን ሰላም ለማናጋት ፈጥረውት የነበረው ጸረ ሰላም እንቅስቃሴ በቁጥጥር ስር እንደዋለ መናገራቸውን ዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል ዘግቧል።]]></description>
            <link>http://www.ectv.org</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <pubDate>Sat, 17 May 2008 09:07:03 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>በውጭ የሚኖሩ የድሬደዋ ተወላጆችና ወዳጆች የሆኑ ኢትዮጵያውያን በድሬደዋ ኢንቨስት ማድረግ ጀመሩ</title>
            <description>ድሬዳዋ ጥር 19/2000/&lt;FONT color=&quot;#FF0033&quot;&gt;ዋኢማ&lt;/FONT&gt;/ በውጭ የሚኖሩ የድሬዳዋ ተወላጆችና ወዳጆች በከተማዋ በተለያዩ የኢንቨስትመንት ዘርፎች መሰማራት ጀመሩ። በሚሊኒየሙ ወደ ሀገራቸው የተመለሱ አንደንድ ኢትዮጵያዊያን ፈቃድ ወስደው የቁም እንስሳትን ወደ ውጭ በመላክ ንግድ መሠማራታቸውን አስታወቁ።&lt;BR&gt;&lt;BR&gt;
በአውሮፓ፣ በአሜሪካ፣ በእስያና በአውስትራሊያ የሚኖሩ የድሬደዋ ተወላጆች ለዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል በሰጡት አስተያየት በሚሊኒየሙ በተፈጠረው መነቃቃት በከተማዋ ኢንቨስትመንት ለመሰማራት አነሳስቷቸዋል።</description>
            <link>http://www.waltainfo.com/AmNews/2008/Jan/28Jan08/42787.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">DB53ECF0-CE7B-11DC-95FC-000393197FB0-475-000000EB02330DC8-FFA</guid>
            <pubDate>Fri, 15 Feb 2008 06:22:06 -0500</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>ድርጅቶቹ ለምርጫው ከ55ሺ በላይ ዕጩዎች ማቅረባቸውን ገለጹ</title>
            <description>አክሱም ጥር 19/2000/ዋኢማ/ በትግራይ ማዕከላዊ ዞን በመጪው ሚያዚያ ወር በሚካሄደው የአካባቢና ማሟያ ምርጫ ህወሐትን ወክለው የሚወዳደሩ 49ሺ 516 ዕጩ ተወዳዳሪዎች በሕዝብ መገምገማቸውን የዞኑ የህዝብ አደረጃጀት ኃላፊ ገለጹ። የብሔረ አማራ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ /ብአዴን/ ለባህር ዳር ከተማ ያዘጋጃቸውን 6ሺ ዕጩዎች በህዝብ እያስገመገመ ነው።</description>
            <link>http://www.waltainfo.com/AmNews/2008/Jan/28Jan08/42779.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">B013D220-CE7B-11DC-95FC-000393197FB0-475-000000EA728A3124-FFA</guid>
            <pubDate>Tue, 29 Jan 2008 10:07:02 -0500</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>በከተሞች በ1 ነጥብ3 ቢሊዮን ብር ወጭ የጋራ መኖሪያ ቤቶች ግንባታ እየተካሄደ ነው</title>
            <description>አዲስ አበባ ጥር 19/2000/ አዲስ አበባና ድሬደዋ አስተዳደሮችን ጨምሮ በሰባት ክልሎች በከተሞች አካባቢ የሚታየውን የመኖሪያ ቤት እጥረት ለማቃለል በ1 ነጥብ 3 ቢሊየን ብር ወጭ የጋራ መኖሪያ ቤቶች ግንባታ እያሄካደ መሆኑን የሥራና ከተማ ልማት ሚኒስቴር አስታወቀ።&lt;br&gt;&lt;br&gt;
ሚኒስትሩ በየክልሎቹ እየተካሄደ ያለውን የቤቶች ልማት ፕሮግራም የግማሽ ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ለመገምገም ዛሬ ባዘጋጀው የውይይት መድረክ ላይ ባቀረበው ሪፖርት እንዳስታወቀው፤ በግማሽ ዓመት ውስጥ የግንባታ ስራቸውን ለመጀመር ከታቀዱት 2ሺ 855 የጋራ መኖሪያ ህንፃዎች መካከል የ2ሺ 290 ህንፃዎች ግንባታቸው ተጀምሯል።</description>
            <link>http://www.waltainfo.com/AmNews/2008/Jan/28Jan08/42785.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">95881DBA-CE7B-11DC-95FC-000393197FB0-475-000000EA1A5DBA25-FFA</guid>
            <pubDate>Tue, 29 Jan 2008 10:05:53 -0500</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>ለአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በ30 ሚሊየን ብር ወጪ የተገነባ ሁለ ገብ ህንፃ ተጠናቆ ርክክብ ተካሄደ</title>
            <description>ለአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በ30 ሚሊየን ብር ወጪ የተገነባ ሁለ ገብ ህንፃ ተጠናቆ ርክክብ ተካሄደ&lt;br&gt;&lt;br&gt;
አዲስ አበባ ጥቅምት 9/1999/ዋኢማ/ ትምህርት ሚኒስቴር ለአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በ30 ሚሊየን ብር ወጪ ያስገነባው ሁለ ገብ ህንፃ ተጠናቆ ርክክብ ተካሄደ። ህንጻው ዩኒቨርስቲው እያካሄደ ላለው የድህረ ምረቃ ፕሮግራሞች ማስፋፊያ እንደሚያግዝ ተገልጿል።</description>
            <link>http://www.waltainfo.com/AmNews/2006/Oct/19Oct06/19461.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">5EA6B2C6-5FB4-11DB-987A-000393197FB0-466-0000001F9D8FD957-FFA</guid>
            <pubDate>Thu, 19 Oct 2006 16:57:45 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>አዲስ አበባን ለሚጎበኙ ቱሪስቶች ጠቃሚ መረጃ የሚሰጥ የአቅጣጫ ጠቋሚ ሶፍትዌር መስራቱን ብላክ ስታር የተባለ ድርጅት ገለጸ</title>
            <description>አዲስ አበባን ለሚጎበኙ ቱሪስቶች ጠቃሚ መረጃ የሚሰጥ የአቅጣጫ ጠቋሚ ሶፍትዌር መስራቱን ብላክ ስታር የተባለ ድርጅት ገለጸ&lt;br&gt;&lt;br&gt;
አዲስ አበባ ጥቅምት 9/1999/ዋኢማ/ የውጭ ቱሪስቶች በአዲስ አበባ ከተማ ለሚያደርጉት እንቅስቃሴ ያለማንም ዕርዳታ ወደ ፈለጉበት ቦታ መዘዋወር ሚያስችላቸው የአቅጣጫ ጠቋሚ ሶፍትዌር መስራቱን ብላክ ስታር የተባለ ድርጅት አስታወቀ። ሶፍትዌሩ የትራፊክ ፍሰትን ለመቆጣጠር የሚረዳ መረጃ እንደሚሰጥም ተመልክቷል።</description>
            <link>http://www.waltainfo.com/AmNews/2006/Oct/19Oct06/19444.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">40B664DE-5FB4-11DB-987A-000393197FB0-466-0000001F3A1E4F02-FFA</guid>
            <pubDate>Thu, 19 Oct 2006 16:57:01 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>በአማራ ክልል ከ5 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ላስመዘገቡ ባለሃብቶች ፈቃድ ተሰጠ</title>
            <description>በአማራ ክልል ከ5 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ላስመዘገቡ ባለሃብቶች ፈቃድ ተሰጠ&lt;br&gt;&lt;br&gt;
ባህርዳር ጥቅምት 9/1999/ ዋኢማ/ በአማራ ክልል ባለፉት ሶስት ወራት 5 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር ካፒታል ያስመዘገቡ ባለሀብቶች ላቀረቧቸው 160 ፕሮጀክቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ መሰጠቱን የክልሉ ኢንቨስትመንት ማስፋፊያ ኤጀንሲ አስታወቀ።</description>
            <link>http://www.waltainfo.com/AmNews/2006/Oct/19Oct06/19442.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">334CB1A1-5FB4-11DB-987A-000393197FB0-466-0000001F0D910546-FFA</guid>
            <pubDate>Thu, 19 Oct 2006 16:56:11 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>አንድ የኦጋዴን ነፃ አውጪ ግንባር ከፍተኛ የአመራር አባል እጃቸውን ለኢትዮጵያ ሰጡ</title>
            <description>አንድ የኦጋዴን ነፃ አውጪ ግንባር ከፍተኛ የአመራር አባል እጃቸውን ለኢትዮጵያ ሰጡ&lt;br&gt;&lt;br&gt;
ጅጅጋ ጥቅምት 9/1999 /ዋኢማ/ የኦጋዴን ነፃ አውጪ ግንባር ማዕከላዊ ኮሚቴ አባልና በግንባሩ የኤርትራና የኬንያ አስተባባሪ የነበሩት አንድ ከፍተኛ አመራር አባል እጃቸውን ለኢትዮጵያ መንግስት መስጠታቸውን የሶማሊ ክልል የፀጥታና ፍትህ ማስተባበሪያ ጠቅላይ ቢሮ አስታወቀ።</description>
            <link>http://www.waltainfo.com/AmNews/2006/Oct/19Oct06/19441.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">24E08676-5FB4-11DB-987A-000393197FB0-466-0000001EDDA936DF-FFA</guid>
            <pubDate>Thu, 19 Oct 2006 16:55:49 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>በኢትዮጵያ የአነስተኛ ብድርና ቁጠባ ባህል እያደገ መምጣቱን ተገለጸ</title>
            <description>በኢትዮጵያ የአነስተኛ ብድርና ቁጠባ ባህል እያደገ መምጣቱን ተገለጸ&lt;br&gt;&lt;br&gt;
አዲስ አበባ ጥቅምት 9/1999/ዋኢማ/ ካለፉት አስር ዓመታት ወዲህ በአገሪቱ የአነስተኛ ብድርና ቁጠባ ባህል እያደገ በመምጣቱ በተያዘው የፈረንጆች ዓመት 1 ነጥብ 7 ሚሊየን ህዝብ የሁለት ቢሊዮን ብር ብድር ተጠቃሚ መሆናቸውን የኢትዮጵያ ማይክሮፋይናንስ ተቋማት ዳይሬክተር ገለጹ። የአዲስ አበባ ብድርና ቁጠባ ተቋምም በመጀመሪያው የሩብ ዓመት ለደንበኞቹ 18 ሚሊየን 500 ሺ ብር ብድር መስጠቱንና አዲስ የማይክሮ ባንክ አገልግሎት መጀመሩን ገልጿል።</description>
            <link>http://www.waltainfo.com/AmNews/2006/Oct/19Oct06/19433.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">12AD594B-5FB4-11DB-987A-000393197FB0-466-0000001EA1356BD6-FFA</guid>
            <pubDate>Thu, 19 Oct 2006 16:55:24 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>ሆላንድ ከኢትዮጵያ ጋር የጀመረችውን ኢኮኖሚክ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ለማጠናከር እየተንቀሳቀሰች ነው</title>
            <description>ሆላንድ ከኢትዮጵያ ጋር የጀመረችውን ኢኮኖሚክ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ለማጠናከር እየተንቀሳቀሰች ነው&lt;br&gt;&lt;br&gt;
አዲስ አበባ ጥቅምት 9/1999/ዋኢማ/ ሆላንድ ከኢትዮጵያ ጋር የጀመረችውን የንግድና ኢንቨስትመንት ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ለማጠናከርና ለማስፋፋት እየተንቀሳቀሰች መሆኑን በኢትዮጵያ የኔዘርላንድ አምባሳደር ገለፁ። በሆላንድ የመኪና መገጣጠሚያ ኩባንያ በ20 ሚሊየን ብር መነሻ ካፒታል በሞጆ ከተማ የተቋቋመው የቤት መኪና መገጣጠሚያ ፋብሪካ ማምረት ጀመረ።</description>
            <link>http://www.waltainfo.com/AmNews/2006/Oct/19Oct06/19437.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">03B50B72-5FB4-11DB-987A-000393197FB0-466-0000001E6F7C2537-FFA</guid>
            <pubDate>Thu, 19 Oct 2006 16:54:54 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>ሮተሪ ኢንተርናሽናል የጸረ ልጅነት ልምሻ የክትባት ዘመቻን ለማጠናከር ድጋፍ እንደሚሰጥ አስታወቀ</title>
            <description>ሮተሪ ኢንተርናሽናል የጸረ ልጅነት ልምሻ የክትባት ዘመቻን ለማጠናከር ድጋፍ እንደሚሰጥ አስታወቀ&lt;br&gt;&lt;br&gt;
አዲስ አበባ ጥቅምት 8/1999/ዋኢማ/ የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ለሚያካሂደው የጸረ ልጅነት ልምሻ መደበኛ ክትባት ዘመቻ ድጋፍ የሚሰጡ 99 የሮተሪ ኢንተርናሽናል አባላት በመጪው ቅዳሜና ዕሁድ በ13 ወረዳዎች የቤት ለቤት ግንዛቤ ለማስጨበጥና ክትባት ለመስጠት ዝግጅት ማድረጋቸውን በሮተሪ ኢንተርናሽናል የብሔራዊ ፖሊዮ ኮሚቴ አስታወቀ።</description>
            <link>http://www.waltainfo.com/AmNews/2006/Oct/19Oct06/19430.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">F4F2CF42-5FB3-11DB-987A-000393197FB0-466-0000001E3E7676D5-FFA</guid>
            <pubDate>Thu, 19 Oct 2006 16:54:29 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዓመቱ የትኩረት አቅጣጫ የፓርላማ አባላት ላነሱዋቸው ጥያቄዎች መልስ ሰጡ</title>
            <description>ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዓመቱ የትኩረት አቅጣጫ የፓርላማ አባላት ላነሱዋቸው ጥያቄዎች መልስ ሰጡ&lt;br&gt;&lt;br&gt;
ጥቅምት 9/1999/ዋኢማ/ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ፕሬዚዳንት ግርማ ወልደጊዮርጊስ በፌደራል ምክር ቤቶች መክፈቻ ባቀረቡት የቀጣይ ዓመት የትኩረት አቅጣጫ ላይ በመንተራስ ለተነሱ ጥያቄዎችና አስተያየቶች ማብራሪያ ሰጡ።</description>
            <link>http://www.waltainfo.com/AmNews/2006/Oct/19Oct06/19455.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">E85E0354-5FB3-11DB-987A-000393197FB0-466-0000001E14AC5AAD-FFA</guid>
            <pubDate>Thu, 19 Oct 2006 16:54:04 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>የዓለማችን የመጨረሻው ግዙፍ የተባለው የኤርባስ አውሮፕላን በአዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ የአየር ማረፊያ ሜዳ ላይ አረፈ</title>
            <description>የዓለማችን የመጨረሻው ግዙፍ የተባለው የኤርባስ አውሮፕላን በአዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ የአየር ማረፊያ ሜዳ ላይ አረፈ&lt;br&gt;&lt;br&gt;
አዲስ አበባ ጥቅምት 7/1999/ዋኢማ/ በዓለም የንግድ የአየር ትራንስፖርት የዓለማችን የመጨረሻው ግዙፍ የተባለው የኤርባስ 380/861 አውሮፕላን በአዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ የአየር ማረፊያ ሜዳ ላይ ማረፉ የአየር መንገዱ የማኮብኮቢያ ሜዳ ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነት ብቃት ያረጋገጠ መሆኑ ተገለፀ።</description>
            <link>http://www.waltainfo.com/AmNews/2006/Oct/17Oct06/19366.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">3C550160-5F02-11DB-9A62-000393197FB0-417-0000000C3416E278-FFA</guid>
            <pubDate>Wed, 18 Oct 2006 19:42:10 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>የአፍሪካ ኅብረት የሰላምና የፀጥታ ምክር ቤት በኮቲዲቭዋር ወቅታዊ ሁኔታ ላይ ተወያየ</title>
            <description>የአፍሪካ ኅብረት የሰላምና የፀጥታ ምክር ቤት በኮቲዲቭዋር ወቅታዊ ሁኔታ ላይ ተወያየ&lt;br&gt;&lt;br&gt;
አዲስ አበባ ጥቅምት 8/1999 የአፍሪካ ኅብረት የሰላምና የፀጥታ ምክር ቤት 64ኛው ስብሰባ የኮቲዲቭዋርን ወቅታዊ ሁኔታ አስመልክቶ በቀረበው ሪፖርት ላይ ውይይት አካሄደ።</description>
            <link>http://www.waltainfo.com/AmNews/2006/Oct/18Oct06/19422.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">2F7C7E9A-5F02-11DB-9A62-000393197FB0-417-0000000C096BDB50-FFA</guid>
            <pubDate>Wed, 18 Oct 2006 19:41:53 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>በሱማሌ ክልል የልማትና የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለመፍታት ቁርጠኛ አመራር መፈጠር እንደሚገባ ተገለጸ</title>
            <description>በሱማሌ ክልል የልማትና የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለመፍታት ቁርጠኛ አመራር መፈጠር እንደሚገባ ተገለጸ&lt;br&gt;&lt;br&gt;
ጅጅጋ ጥቅምት 8/1999/ዋኢማ የሱማሌ ክልል የልማትና የመልካም አስተዳደር ችግሮች ለመፍታት ቁርጠኛ አመራሮች መፈጠር እንዳለባቸው የክልሉ ርዕስ መስተዳድር ገለፁ።</description>
            <link>http://www.waltainfo.com/AmNews/2006/Oct/18Oct06/19397.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">1911AAC6-5F02-11DB-9A62-000393197FB0-417-0000000BBEF5ECDB-FFA</guid>
            <pubDate>Wed, 18 Oct 2006 19:41:32 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>ዩኒቨርሲቲው የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ዕቅድ ማዘጋጀቱን ገለጸ</title>
            <description>ዩኒቨርሲቲው የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ዕቅድ ማዘጋጀቱን ገለጸ&lt;br&gt;&lt;br&gt;
መቀሌ ጥቅምት 8/1999/ዋኢማ/ የመቀሌ ዩኒቨርሲቲ የትምህርት ጥራትን በማረጋገጥ ብቁ የተማረ ዜጋ ለማፍራት የሚያስችል የ20 ዓመት ስትራቴጂክ ዕቅድ አውጥቶ በመንቀሳቀስ ላይ መሆኑን አስታወቀ።</description>
            <link>http://www.waltainfo.com/AmNews/2006/Oct/18Oct06/19387.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">03292902-5F02-11DB-9A62-000393197FB0-417-0000000B7630DCE4-FFA</guid>
            <pubDate>Wed, 18 Oct 2006 19:40:54 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>ኢህአዴግ ለአባላቱ የአመራር ስልጠና እንደሚሰጥ ገለጸ</title>
            <description>ኢህአዴግ ለአባላቱ የአመራር ስልጠና እንደሚሰጥ ገለጸ&lt;br&gt;&lt;br&gt;
አዲስ አበባ ጥቅምት 8/1999/ዋኢማ/የኢህአዴግ ፅህፈት ቤት ብቃትና ጥራት ያለው አመራር ለመፍጠርና መልካም አስተዳደርን ለማስፈን የሚያስችል ተከታታይ የአመራር ስልጠና እንዲሚሰጥ አስታወቀ።የመጀመሪያው ዙር የከፍተኛ አመራር አካላት ስልጠና ጥቅምት 15 እንደሚጀመር ተገልጿል።</description>
            <link>http://www.waltainfo.com/AmNews/2006/Oct/18Oct06/19409.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">F52E56D0-5F01-11DB-9A62-000393197FB0-417-0000000B47C18C82-FFA</guid>
            <pubDate>Wed, 18 Oct 2006 19:40:17 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>ለውጭ ገበያ የሚላከው የቁም እንስሳትና የስጋ ምርት አቅርቦትን ለማሳደግ አዋጭ የሆነ መንገድ መከተል እንደሚገባ ተገለጸ</title>
            <description>ለውጭ ገበያ የሚላከው የቁም እንስሳትና የስጋ ምርት አቅርቦትን ለማሳደግ አዋጭ የሆነ መንገድ መከተል እንደሚገባ ተገለጸ&lt;br&gt;&lt;br&gt;
አዲስ አበባ ጥቅምት 8/1999/ዋኢማ/ ለውጭ ገበያ የሚላከው የቁም እንስሳትና የስጋ ምርት አቅርቦትን በተያዘለት ዕቅድ ለማስኬድ አዋጭ የሆነ መንገድ መከተል እንደሚገባ የግብርናና ገጠር ልማት ሚኒስቴር አስታወቀ። በተያዘው የመጀመሪያው ሩብ የበጀት ዓመት ከ39 ሺ በላይ የቁም እንስሳትና የከ1 ሺ 200 ቶን በላይ ስጋና የስጋ ውጤቶች ወደ ተለያዩ ዓለም አገራት መላካቸው ተገልጿል።</description>
            <link>http://www.waltainfo.com/AmNews/2006/Oct/18Oct06/19424.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">E30099CF-5F01-11DB-9A62-000393197FB0-417-0000000B0B5FD1C8-FFA</guid>
            <pubDate>Wed, 18 Oct 2006 19:39:54 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>ሥርዓተ- ጾታን ማዕከል ያደረገ የልማት እንቅስቃሴ ለኢኮኖሚ እድገት ወሳኝ ድርሻ እንዳለው ተገለጸ</title>
            <description>ሥርዓተ- ጾታን ማዕከል ያደረገ የልማት እንቅስቃሴ ለኢኮኖሚ እድገት ወሳኝ ድርሻ እንዳለው ተገለጸ&lt;br&gt;&lt;br&gt;
አዳማ ጥቅምት 8/1999/ዋኢማ/ ሥርዓተ ጾታን ማዕከል አድርጎ የሚተገበር ማንኛውም የልማት እንቅስቃሴ ለኢኮኖሚ እድገት ወሳኝ ድርሻ እንዳለው የውሀ ሀብት ሚኒስቴር አስታወቀ።</description>
            <link>http://www.waltainfo.com/AmNews/2006/Oct/18Oct06/19421.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">DA346331-5F01-11DB-9A62-000393197FB0-417-0000000AEE26EE19-FFA</guid>
            <pubDate>Wed, 18 Oct 2006 19:39:24 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>በትግራይ የአመራር አካላት በመልካም አስተዳደር የሚታዩ ችግሮችን ለመፍታት ተኩረት ሰጥተው እነደሚሠሩ ተገለፀ</title>
            <description>በትግራይ የአመራር አካላት በመልካም አስተዳደር የሚታዩ ችግሮችን ለመፍታት ተኩረት ሰጥተው እነደሚሠሩ ተገለፀ&lt;br&gt;&lt;br&gt;
መቀሌ ጥቅምት 2/1999/ዋኢማ/ በተያዘው አዲስ ዓመት የመንግሥት አመራር አካላት በመልካም አስተዳደርና በፍትሕ የሚታዩ ችግሮችን ለመፍታት ትኩረት ሰጥተው መሥራት እንዳለባቸው የትግራይ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አስገነዘቡ።</description>
            <link>http://www.waltainfo.com/AmNews/2006/Oct/12Oct06/19182.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">70D18F7B-5A56-11DB-932E-000393197FB0-409-0000013A41E8C8A6-FFA</guid>
            <pubDate>Thu, 12 Oct 2006 21:02:37 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>ዩኒሴፍ በሕፃናት ጤና ክብካቤ የሚየካሂደውን ድጋፍ በአሥር እጥፍ ሊያሳድግ ነው</title>
            <description>ዩኒሴፍ በሕፃናት ጤና ክብካቤ የሚየካሂደውን ድጋፍ በአሥር እጥፍ ሊያሳድግ ነው&lt;br&gt;&lt;br&gt;&lt;a href=&quot;http://www.waltainfo.com/AmNews/2006/Oct/12Oct06/19180.htm&quot;&gt;&lt;img src=&quot;http://www.waltainfo.com/Resource/UNICEF.jpg&quot;&gt;&lt;/a&gt;
አዋሳ ጥቅምት 2/1999/ዋኢማ/በተባበሩት መንግሥታት የሕፃናት መርጃ ድርጅት /ዩኒሴፍ/በመጪው አዲስ የፈረንጆች ዓመት በሕፃናት መብትና ጤና ክብካቤ ዙሪያ በኢትዮጵያ የሚያካሂዳቸውን ፕሮጄክቶች በአሥር እጥፍ ለማሳደግ መዘጋጀቱን አስታወቀ።</description>
            <link>http://www.waltainfo.com/AmNews/2006/Oct/12Oct06/19180.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">33FC6E84-5A56-11DB-932E-000393197FB0-409-0000013977D982BF-FFA</guid>
            <pubDate>Thu, 12 Oct 2006 21:02:01 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>በጋንቤላ ክልል በግንዛቤ ማነስ የሲቪል ሰርቪስ ማሻሻያ ፕሮግራሙን መተግበር እንዳልተቻለ ተገለጸ</title>
            <description>በጋንቤላ ክልል በግንዛቤ ማነስ የሲቪል ሰርቪስ ማሻሻያ ፕሮግራሙን መተግበር እንዳልተቻለ ተገለጸ&lt;br&gt;&lt;br&gt;
ጋምቤላ ጥቅምት 2/1999/ዋኢማ / ፈጣንና ህዝባዊ አገልግሎት ለመስጠት ታስቦ የተነደፈው የሲቪል ሰርቪስ ማሻሻያ ፕሮግራሙን ለመተግበር የክልሉ አመራር ያለው ግንዛቤ ዝቅተኛ በመሆኑ የተፈለገውን ያህል ውጤት ሊመጣ እንዳልቻለ የጋምቤላ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳደር አስታወቁ።</description>
            <link>http://www.waltainfo.com/AmNews/2006/Oct/12Oct06/19155.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">25C588F4-5A56-11DB-932E-000393197FB0-409-0000013948A2A57C-FFA</guid>
            <pubDate>Thu, 12 Oct 2006 21:00:21 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>የሉሜ - አዳማ ገበሬዎች ኅብረት ሥራ ዩኒየን የአርሶ አደሩንና የሸማቹን ገበያ ለማረጋጋት በ16 ሚሊየን ብር የእህል ግዥ ጀመረ</title>
            <description>የሉሜ - አዳማ ገበሬዎች ኅብረት ሥራ ዩኒየን የአርሶ አደሩንና የሸማቹን ገበያ ለማረጋጋት በ16 ሚሊየን ብር የእህል ግዥ ጀመረ&lt;br&gt;&lt;br&gt;
አዲስ አበባ ጥቅምት 2/1999/ዋኢማ/ በኦሮሚያ ክልል የሉሜ - አዳማ ገበሬዎች ኅብረት ሥራ ዩኒየን የአርሶ አደሩንና የሸማቹን ገበያ ለማረጋጋት በመደበው 16 ሚሊየን ብር የእህል ግዥ መጀመሩን አስታወቀ። ባሁኑ ወቅት ለዓለም ገበያ የሚያቀርበው 80 ሺ ኩንታል ቦለቄ ግዥ በማካሄድ ላይ መሆኑን ገልጿል።</description>
            <link>http://www.waltainfo.com/AmNews/2006/Oct/12Oct06/19147.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">0215491E-5A56-11DB-932E-000393197FB0-409-00000138D217EE12-FFA</guid>
            <pubDate>Thu, 12 Oct 2006 20:59:26 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>ቢሮው ከ16ሺ በላይ ወገኖች የፀረ ኤች አይቪ መድሃኒት በነፃ እየሰጠ መሆኑን ገለፀ</title>
            <description>ቢሮው ከ16ሺ በላይ ወገኖች የፀረ ኤች አይቪ መድሃኒት በነፃ እየሰጠ መሆኑን ገለፀ&lt;br&gt;&lt;br&gt;
አዲስ አሰበባ ጥቅምት 2/1999/ዋኢማ /ከኤችአይቪ/ኤድስ ጋር ለሚኖሩ ከ16ሺ በላይ ወገኖች የፀረ ኤች አይ ቪ /ኤድስ መድሃኒት በ15 የጤና ማዕከላት በነፃ በመሰጠት ላይ መሆኑን የአዲስ አበባ ጤና ቢሮ አስታወቀ ።</description>
            <link>http://www.waltainfo.com/AmNews/2006/Oct/12Oct06/19192.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">ED76A278-5A55-11DB-932E-000393197FB0-409-000001388D9A820E-FFA</guid>
            <pubDate>Thu, 12 Oct 2006 20:58:58 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>ማህበሩ የስነተዋልዶ ጤናና ቤተሰብ ምጣኔ አገልግሎትን ለማጠናከርና የሚያስችል ፕሮጀክት ይፋ አደረገ</title>
            <description>ማህበሩ የስነተዋልዶ ጤናና ቤተሰብ ምጣኔ አገልግሎትን ለማጠናከርና የሚያስችል ፕሮጀክት ይፋ አደረገ&lt;br&gt;&lt;br&gt;
አዲስ አበባ ጥቀምት 2/1999 /ዋኢማ/ የኢትዮጵያ ጤና አጠባበቅ ማህበር በአማራ ክልል ሁለት ዞኖች የስነተዋልዶ ጤናና ቤተሰብ ምጣኔ አገልግሎትን ለማጠናከርና ለማሻሻል የሚያስችል ፕሮጀክት ይፋ አደረገ፡፡ፕሮጀክቱ ከፓካርድ ፋውንዴሽን ባገኘው 1 ሚሊዮን ዶላር ለሶስት አመታት የሚከናወን ነው፡፡</description>
            <link>http://www.waltainfo.com/AmNews/2006/Oct/12Oct06/19173.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">DED38A03-5A55-11DB-932E-000393197FB0-409-000001385CFC424A-FFA</guid>
            <pubDate>Thu, 12 Oct 2006 20:58:23 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>ሰዎች ለሰዎች ከክልሉ ጽህፈት ቤትጋር የ39 ሚሊየን ብር የእርዳታ ስምምነት ተፈራረመ</title>
            <description>ሰዎች ለሰዎች ከክልሉ ጽህፈት ቤትጋር የ39 ሚሊየን ብር የእርዳታ ስምምነት ተፈራረመ&lt;br&gt;&lt;br&gt;
አዲስ አበባ ጥቅምት 2/1999/ዋኢማ/ የአማራ ክልል የምግብ ዋስትናና አደጋ መከላከል ጽህፈት ቤት የአሳግርት ወረዳን የልማት እንቅስቃሴ የሚያግዝ የ39 ሚሊዮን ብር የልማት ስምምነት ሰዎች ለሰዎች ከተባለ ግብረሰናይ ድርጅት ጋር ተፈራረመ፡፡የልማት ስምምነቱ ለሶስት አመታት የሚቆይ ሲሆን 54 ሺ ሰዎቸን ተጠቃሚ ያደርጋል፡፡</description>
            <link>http://www.waltainfo.com/AmNews/2006/Oct/12Oct06/19188.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">CF75FF76-5A55-11DB-932E-000393197FB0-409-0000013829F2B71B-FFA</guid>
            <pubDate>Thu, 12 Oct 2006 20:57:58 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>በበጀት ዓመቱ በሁለት ቢሊየን ብር ወጪ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የሚያስቸሉ የልማት ስራዎች እንደሚከናወኑ ተገለፀ</title>
            <description>በበጀት ዓመቱ በሁለት ቢሊየን ብር ወጪ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የሚያስቸሉ የልማት ስራዎች እንደሚከናወኑ ተገለፀ&lt;br&gt;&lt;br&gt;
አዲስ አበባ ጥቅምት 2/1999/ዋኢማ/ በተያዘው የበጀት ዓመት የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ለሚካሄዱ የተለያዩ የልማት ስራዎች ማስፈፀሚያ በፌዴራል መንግስት ሁለት ቢሊየን ብር ተመድቦ እንቅስቃሴ መጀመሩን በግብርናና ገጠር ልማት ሚኒስቴር የምግብ ዋስትና ማስተባበሪያ ቢሮ አስታወቀ። ዘንድሮ ለአምስተኛ ጊዜ በሚካሄደው የሰፈራ ፕሮግራም 40 ሺ የቤተሰብ መሪ አርሶ አደሮችን የተሻለ ለምነት ወዳላቸው አካባቢዎች በፈቃደኝነት ለማስፈር መታቀዱንም አመልክቷል።</description>
            <link>http://www.waltainfo.com/AmNews/2006/Oct/12Oct06/19174.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">C0D2F92F-5A55-11DB-932E-000393197FB0-409-00000137F954B44E-FFA</guid>
            <pubDate>Thu, 12 Oct 2006 20:57:33 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ በቪዲዮ ኮንፈረንስ አማካይነት ፈጣን የፍትህ አገልግሎት መስጠት መጀመሩን ተገለፀ</title>
            <description>ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ በቪዲዮ ኮንፈረንስ አማካይነት ፈጣን የፍትህ አገልግሎት መስጠት መጀመሩን ተገለፀ&lt;br&gt;&lt;br&gt;
መቀሌ ጥቅምት 2/1999/ዋኢማ/ የትግራይ ክልል ጠቅላይ ፍድ ቤት በቪድዮ ኮንፈረንስ አማካይነት ለህብረተሰቡ ፈጣን የፍትህ አገልግሎት መስጠት መጀመሩን ገለፀ ።</description>
            <link>http://www.waltainfo.com/AmNews/2006/Oct/12Oct06/19152.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">AC27085E-5A55-11DB-932E-000393197FB0-409-00000137B4AB22A6-FFA</guid>
            <pubDate>Thu, 12 Oct 2006 20:57:08 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>ፌዴራል ፖሊስ አገራዊ ሀላፊነቱን ለመወጣት ህብረ ብሄራዊ አደረጃጀቱን ማጠናከር እንደሚኖርበት ተጠቆመ</title>
            <description>ፌዴራል ፖሊስ አገራዊ ሀላፊነቱን ለመወጣት ህብረ ብሄራዊ አደረጃጀቱን ማጠናከር እንደሚኖርበት ተጠቆመ&lt;br&gt;&lt;br&gt;
አዲስ አበባ ጥቅምት 2/1999/ዋኢማ /የፌዴራል ፖሊስ ተቋማት በህግ የተጣለባቸውን አገራዊ ሀላፊነት በብቃት ለመወጣት እንዲችሉ ህብረ ብሄራዊ አደረጃጀታቸውን ማጠናከርና ለዲሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ መሳሪያ መሆን እንደሚጠበቅባቸው አንድ ምሁር ገለፁ።</description>
            <link>http://www.waltainfo.com/AmNews/2006/Oct/12Oct06/19167.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">97FE4D14-5A55-11DB-932E-000393197FB0-409-0000013771B5648B-FFA</guid>
            <pubDate>Thu, 12 Oct 2006 20:56:33 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>ሪጅኑ በ126 ሚሊየን ብር በሶስት ክልሎች የተለያየ የስልክ መስመር መዘርጋት ስራ እያከናወነ ነው</title>
            <description>ሪጅኑ በ126 ሚሊየን ብር በሶስት ክልሎች የተለያየ የስልክ መስመር መዘርጋት ስራ እያከናወነ ነው&lt;br&gt;&lt;br&gt;&lt;a href=&quot;http://www.waltainfo.com/AmNews/2006/Oct/12Oct06/19146.htm&quot;&gt;&lt;img src=&quot;http://www.waltainfo.com/Resource/ETC.jpg&quot;&gt;&lt;/a&gt;
አዳማ ጥቅምት 2/1999 ዋኢማ/ የኢትዮጵያ ቴሌኮሙኒኬሽን ኮርፖሬሽን የደቡብ ምሥራቅ ሪጅን ከ126 ሚሊየን ብር በላይ በጀት በሶስት ክልሎች የዲጅታል ቴሌፎን የማዞሪያ ኔት ወርክና የኦፕቲካል ፋይበር መስመር የመዘርጋት ተግባራትን እያከናወነ መሆኑን አስታወቀ።</description>
            <link>http://www.waltainfo.com/AmNews/2006/Oct/12Oct06/19146.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">33DD487E-5A55-11DB-932E-000393197FB0-409-00000136251F7639-FFA</guid>
            <pubDate>Thu, 12 Oct 2006 20:55:55 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>በጢያራ ከተማ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብተው ለአገልግሎት መብቃታቸው ተገለፀ</title>
            <description>በጢያራ ከተማ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብተው ለአገልግሎት መብቃታቸው ተገለፀ&lt;br&gt;&lt;br&gt;
መቀሌ ጥቅምት 2/1999/ዋኢማ/በዓፋር ክልል በራሕሌ ወረዳ በጢያራቦራ ከተማ ከ14 ሚሊየን ብር በላይ በሆነ ወጭ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተገንብተው ለአገልግሎት መብቃታቸውን የወረዳው አስተዳደር ገለፀ።</description>
            <link>http://www.waltainfo.com/AmNews/2006/Oct/12Oct06/19145.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">1DD9FBC4-5A55-11DB-932E-000393197FB0-409-00000135DC0167BA-FFA</guid>
            <pubDate>Thu, 12 Oct 2006 20:53:12 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>ወደ ኬኒያ የሚፈልሱ የሶማሊያ ስደተኞች ቁጥር በፍጥነት እየጨመረ መምጣቱ ተገለፀ</title>
            <description>ወደ ኬኒያ የሚፈልሱ የሶማሊያ ስደተኞች ቁጥር በፍጥነት እየጨመረ መምጣቱ ተገለፀ&lt;br&gt;&lt;br&gt;
አዲስ አበባ ጥቅምት 2/1999/ዋኢማ/በሶማሊያ ያለው ውጥረት የሚባባስ ከሆነ በተያዘው የፈረንጆች አመት መጨረሻ ወደ ኬኒያ የሚፈልሱ የሶማሊያ ስደተኞች ቁጥር 80 ሺ ሊደርስ እንደሚችል አንድ የተባበሩት መንግስታት ባለስልጣን አስጠነቀቁ፡፡</description>
            <link>http://www.waltainfo.com/AmNews/2006/Oct/12Oct06/19186.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">0E0183A8-5A55-11DB-932E-000393197FB0-409-00000135A75F8C3A-FFA</guid>
            <pubDate>Thu, 12 Oct 2006 20:52:35 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>የሶማሊያ እስላማዊ ፍርድ ቤት የመገናኛ ብዙሀንን የሚገድብ ደንብ ማውጣቱ ውግዘት ገጠመው</title>
            <description>የሶማሊያ እስላማዊ ፍርድ ቤት የመገናኛ ብዙሀንን የሚገድብ ደንብ ማውጣቱ ውግዘት ገጠመው&lt;br&gt;&lt;br&gt;
አዲስ አበባ ጥቅምት 2/1999/ዋኢማ/ የሶማሊያ እስላማዊ ፍርድ ቤት የመገናኛ ብዙሀንን የሚገድብ ደንብ ማውጣቱን እንደሚቃወም ዓለም አቀፍ ድንበር የለሽ የጋዜጠኞች ቡድን አስታወቀ።</description>
            <link>http://www.waltainfo.com/AmNews/2006/Oct/12Oct06/19185.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">03E84346-5A55-11DB-932E-000393197FB0-409-0000013585D47459-FFA</guid>
            <pubDate>Thu, 12 Oct 2006 20:52:08 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>በክልሉ ህዝቡን የመልካም አስተዳደር ተጠቃሚ ለማድረግ አስፈፃሚ አካላት ርብርብ ማድረግ እንዳለባቸው ተገለጸ</title>
            <description>በክልሉ ህዝቡን የመልካም አስተዳደር ተጠቃሚ ለማድረግ አስፈፃሚ አካላት ርብርብ ማድረግ እንዳለባቸው ተገለጸ&lt;br&gt;&lt;br&gt;
ባህርዳር መስከረም 28/1999/ዋኢማ/ በአማራ ክልል ዴሞክራሲን፣ የመልካም አስተዳደርንና ሲቪል ሰርቪስ ሪፎርምን በሁሉም የመንግስት እርከኖች ተግባራዊ ለማድረግ አስፈፃሚ አካላት ከመቼውም ይበልጥ ሊረባረቡ እንደሚገባ የክልሉ ዓቅም ግንባታ ቢሮ አሳሰበ።</description>
            <link>http://www.waltainfo.com/AmNews/2006/Oct/08Oct06/19004.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">A356C856-57E6-11DB-B1BB-000393197FB0-420-000000E4AC302312-FFA</guid>
            <pubDate>Mon, 09 Oct 2006 18:37:22 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ለዘላቂ የውሃ ዕድገትና አጠቃቀም የሚያግዙ ምርምሮችን እያካሄደ መሆኑ ተገለጸ</title>
            <description>የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ለዘላቂ የውሃ ዕድገትና አጠቃቀም የሚያግዙ ምርምሮችን እያካሄደ መሆኑ ተገለጸ&lt;br&gt;&lt;br&gt;
አርባምንጭ መስከረም 28/1999/ዋኢማ/ የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ለአገሪቱ ዘላቂ የውሃ ዕድገትና አጠቃቀም የሚያግዙ ምርምሮችን እያካሄደ መሆኑን ገለፀ። ዩኒቨርሲቲው ዘላቂ የውሃ ዕድገትና አጠቃቀም በሚል ርዕስ ነገ ሃገር አቀፍ ሲምፖዚየም ያካሂዳል።</description>
            <link>http://www.waltainfo.com/AmNews/2006/Oct/08Oct06/19002.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">9795ABC6-57E6-11DB-B1BB-000393197FB0-420-000000E485252816-FFA</guid>
            <pubDate>Mon, 09 Oct 2006 18:36:42 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>የሐረማያ ዩኒቨርስቲ ለምግብ ዋስትና ዕገዛ የሚያደርጉ 126 የምርምር ፕሮጀክቶች በማካሔድ ላይ ነው</title>
            <description>የሐረማያ ዩኒቨርስቲ ለምግብ ዋስትና ዕገዛ የሚያደርጉ 126 የምርምር ፕሮጀክቶች በማካሔድ ላይ ነው&lt;br&gt;&lt;br&gt;
ሐረር መስከረም 28/1999/ዋኢማ/ የሐረማያ ዩኒቨርስቲ በተያዘው የፈረንጆች ዓመት ለምግብ ዋስትና ዕገዛ የሚያደርጉ 126 ነባርና አዲስ የምርምርና ጥናት ፕሮጀክቶችን በማካሔድ ላይ መሆኑን አስታወቀ።</description>
            <link>http://www.waltainfo.com/AmNews/2006/Oct/08Oct06/19001.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">5597C87C-57E6-11DB-B1BB-000393197FB0-420-000000E3A9F2E1D8-FFA</guid>
            <pubDate>Mon, 09 Oct 2006 18:36:23 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>ማዕከሉ ምርታማነትን ለማሳደግ የሚያስችሉ ሁለት የተሻሻሉ የቦሎቄ ዝርያዎችን በምርምር አገኘ</title>
            <description>ማዕከሉ ምርታማነትን ለማሳደግ የሚያስችሉ ሁለት የተሻሻሉ የቦሎቄ ዝርያዎችን በምርምር አገኘ&lt;br&gt;&lt;br&gt;
አዋሳ መስከረም 29/1999/ዋኢማ/ የአረካ ግብርና ምርምር ማዕከል የአረሶ አደደሩን ምርታማነት ለማሳደግ የሚያስችሉ ሁለት አዳዲስና የተሻሻሉ የቦሌቄ ዝርያዎችን በምርምር ማግኘቱን አስታወቀ።</description>
            <link>http://www.waltainfo.com/AmNews/2006/Oct/09Oct06/19050.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">423CA45C-57E6-11DB-B1BB-000393197FB0-420-000000E369A8058F-FFA</guid>
            <pubDate>Mon, 09 Oct 2006 18:34:32 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>የአዋሽ ብሄራዊ ፓርክ በ9 ሺ 68 ቱሪስቶች ተጎበኘ</title>
            <description>የአዋሽ ብሄራዊ ፓርክ በ9 ሺ 68 ቱሪስቶች ተጎበኘ&lt;br&gt;&lt;br&gt;
አዲስ አበባ መስከረም 29/1999/ዋኢማ/ ባለፈው የበጀት ዓመት 9 ሺ 68 ቱሪስቶች የአዋሽ ብሄራዊ ፓርክ መጎብኘታቸውን የፓርኩ ጽህፈት ቤት አስታወቀ። ከቱሪስቶች የሚገኘው ገቢም በዕጥፍ ጨምሯል።</description>
            <link>http://www.waltainfo.com/AmNews/2006/Oct/09Oct06/19049.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">3472132A-57E6-11DB-B1BB-000393197FB0-420-000000E33BD8FB9F-FFA</guid>
            <pubDate>Mon, 09 Oct 2006 18:33:59 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>የአርሶ አደሩን ባህላዊ ዕውቀቶች ለዘላቂ የግብርና ልማት እንደ ግብአት መጠቀም እንደሚያስፈልግ ተጠቆመ</title>
            <description>የአርሶ አደሩን ባህላዊ ዕውቀቶች ለዘላቂ የግብርና ልማት እንደ ግብአት መጠቀም እንደሚያስፈልግ ተጠቆመ&lt;br&gt;&lt;br&gt;
አዲስ አበባ መስከረም 29/1999 /ዋኢማ / በየአካባቢው የሚገኙ የአርሶ አደሩን ባህላዊ ዕውቀቶች ለዘላቂ የግብርና ልማትና የመሬት አጠቃቀም ስትራቴጂ ስኬት እንደ ግብአት ለመጠቀም የተጀመረው ጥረት ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት የግብርናና ገጠር ልማት ሚኒስትር ዴኤታ አስታወቁ።</description>
            <link>http://www.waltainfo.com/AmNews/2006/Oct/09Oct06/19048.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">C723174F-57E5-11DB-B1BB-000393197FB0-420-000000E1D0C57DC7-FFA</guid>
            <pubDate>Mon, 09 Oct 2006 18:33:36 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>የአርባ ምንጭ ዩኒቨርስቲ ለምርምር ስራዎች 500 ሺ ብር የሚደርስ በጀት መድቦ በመንቀሳቀስ ላይ ነው</title>
            <description>የአርባ ምንጭ ዩኒቨርስቲ ለምርምር ስራዎች 500 ሺ ብር የሚደርስ በጀት መድቦ በመንቀሳቀስ ላይ ነው&lt;br&gt;&lt;br&gt;
አርባ ምንጭ መስከረም29/1999/ዋኢማ/ የአርባ ምንጭ ዩኒቨርስቲ በዘንድሮ ዓመት ለሚያካሂዳቸው 12 የምርምር ፕሮጀክቶች እስከ 500 ሺ ብር የሚደርስ በጀት መድቦ በመንቀሳቀስ ላይ መሆኑን አስታወቀ።</description>
            <link>http://www.waltainfo.com/AmNews/2006/Oct/09Oct06/19041.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">BCEC297C-57E5-11DB-B1BB-000393197FB0-420-000000E1AED7CBA4-FFA</guid>
            <pubDate>Mon, 09 Oct 2006 18:30:33 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>የመምህራን የደረጃ እድገት መፈቀዱ መንግስት ለሙያው የሰጠውን ክብር እንደሚያሳይ ተገለጸ</title>
            <description>የመምህራን የደረጃ እድገት መፈቀዱ መንግስት ለሙያው የሰጠውን ክብር እንደሚያሳይ ተገለጸ&lt;br&gt;&lt;br&gt;
አሶሳ መስከረም 29/1999/ዋኢማ/መንግስት ተቋርጦ የቆየው የመምህራን የደረጃ እድገት መፍቀዱ የመምህሩን የኢኮኖሚ አቅም ከማጠናከር ባሻገር ብቁ ዜጋን ለማፍራት ለሚያደርገው ጥረት አጋዥ ነው ሲል የቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል የመምህራን ማህበር አስታወቀ፡፡</description>
            <link>http://www.waltainfo.com/AmNews/2006/Oct/09Oct06/19040.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">AB2EDB18-57E5-11DB-B1BB-000393197FB0-420-000000E173EB84A6-FFA</guid>
            <pubDate>Mon, 09 Oct 2006 18:30:16 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>በወረዳው በጥቃቅንና አነስተኛ ንግድ የተሰማሩ ወገኖች 7ሺ ለሚጠጉ ወገኖች የስራ እድል መፍጠራቸው ተገለጸ</title>
            <description>በወረዳው በጥቃቅንና አነስተኛ ንግድ የተሰማሩ ወገኖች 7ሺ ለሚጠጉ ወገኖች የስራ እድል መፍጠራቸው ተገለጸ&lt;br&gt;&lt;br&gt;
አክሱም መስከረም 29/1999 /ዋኢማ/ በትግራይ ሰሜናዊ ምዕራብ ዞን በሽሬ እንዳስላሴ ወረዳ በጥቃቅንና አነስተኛ ንግድ የተሰማሩ ወገኖች 7ሺ ለሚጠጉ ነዋሪዎች የስራ እድል መፍጠራቸውን የወረዳው አስተዳደር አስታወቀ።ተቋማቱ ለእርሻው ክፍለ ኢኮኖሚ አጋዥ የሆኑ የተለያዩ የእርሻ መሳሪያዎች በተመጣጣኝ ዋጋ እያቀረቡ መሆናቸው ተገልጿል።</description>
            <link>http://www.waltainfo.com/AmNews/2006/Oct/09Oct06/19039.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">9C695536-57E5-11DB-B1BB-000393197FB0-420-000000E142DAE9C5-FFA</guid>
            <pubDate>Mon, 09 Oct 2006 18:29:46 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>ድርጅቱ በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ መሰረታዊ ለውጥ ለማምጣት የሚያስችለው እንቅስቃሴ መጀመሩን ገለጸ</title>
            <description>ድርጅቱ በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ መሰረታዊ ለውጥ ለማምጣት የሚያስችለው እንቅስቃሴ መጀመሩን ገለጸ&lt;br&gt;&lt;br&gt;
አዲስ አበባ መስከረም 29/1999/ዋኢማ/ የኢትዮጵያ ፖስታ አገልግሎት ድርጅት መሰረታዊ የአገልግሎት አሰጣጥ ለውጥ ለማምጣት ባካሄደው ጥናት መሰረት በተያዘው የበጀት ዓመት አዳዲስ አሰራሮችን ተግባራዊ እንደሚያደርግ አስታወቀ። የዘንድሮው የዓለም ፖስታ ቀን “በደንበኞች መታመንን ለማትረፍ ጥራት ያለውን አገልግሎት በሙሉዕነት ማቅረብ” በሚል መርህ ዛሬ ለ35ኛ ጊዜ ተከብሮ መዋሉንም ገለፀ።</description>
            <link>http://www.waltainfo.com/AmNews/2006/Oct/09Oct06/19037.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">8B632EAD-57E5-11DB-B1BB-000393197FB0-420-000000E10A4F0020-FFA</guid>
            <pubDate>Mon, 09 Oct 2006 18:29:21 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>የሱማሌ ክልል ገቢ የመሰብሰብ አቅሙን ለማሳደግ የተለያዩ ስልቶች መቀየሱን አስታወቀ</title>
            <description>የሱማሌ ክልል ገቢ የመሰብሰብ አቅሙን ለማሳደግ የተለያዩ ስልቶች መቀየሱን አስታወቀ&lt;br&gt;&lt;br&gt;
ጅጅጋ መስከረም 29/1999/ዋኢማ /በሱማሌ ክልል በዝቅተኛ ደረጃ የሚገኘውን የገቢ አቅም ለማሳደግ የተለያዩ የገቢ ማሰባሰቢያ ስልቶችን ተግባራዊ በማድረግ ላይ መሆኑን የክልሉ ገቢዎች ቢሮ ገለፀ።ከገቢ አሰባሰብ ጋር በተያያዘ ህግ ወጥ ስራ በሚፈፅሙ ሰራተኞችና ተባባሪዎች ላይ የማስተካከያ እርምጃ እንደሚወሰድም አስታወቋል።</description>
            <link>http://www.waltainfo.com/AmNews/2006/Oct/09Oct06/19052.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">6EE2DA52-57E5-11DB-B1BB-000393197FB0-420-000000E0ABA3B698-FFA</guid>
            <pubDate>Mon, 09 Oct 2006 18:28:25 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>የውሃ ሃብት በምግብ እህል እራስን ለማቻል ዋነኛ መሳሪያ መሆኑ ተገለፀ</title>
            <description>የውሃ ሃብት በምግብ እህል እራስን ለማቻል ዋነኛ መሳሪያ መሆኑ ተገለፀ&lt;br&gt;&lt;br&gt;
አርባ ምንጭ መስከረም 29/1999/ዋኢማ/ ድህነትን ለመቀነስና በምግብ እህል ራስን ለመቻል ጉልህ ድርሻ ያለውን የውሃ ሃብት ልማት ተኮር በሆኑ ዘዴዎች መጠቀም ተገቢ መሆኑን ተገለፀ። በዘላቂ የውሃ ዕድገትና አጠቃቀም ላይ የሚነጋገር አገር አቀፍ ሲንፖዚየም ዛሬ በአርባ ምንጭ ዩኒቨርስቲ ተጀምሯል።</description>
            <link>http://www.waltainfo.com/AmNews/2006/Oct/09Oct06/19057.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">562FBCDE-57E5-11DB-B1BB-000393197FB0-420-000000E0599907BD-FFA</guid>
            <pubDate>Mon, 09 Oct 2006 18:28:05 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>ለአሥር ዓመታት የሚያገለግል የመቀሌ ከተማ ማስተር ፕላን ሥራ መጠናቀቁ ተገለፀ</title>
            <description>ለአሥር ዓመታት የሚያገለግል የመቀሌ ከተማ ማስተር ፕላን ሥራ መጠናቀቁ ተገለፀ&lt;br&gt;&lt;br&gt;
መቀሌ መስከረም 29/1999/ዋኢማ/የመቀሌ ከተማ የአሥር ዓመት ማስተር ፕላን ፕሮጀክት ሥራ ተጠናቅቆ ለአገልግሎት መዘጋጀቱን የከተማዋ ማዛጋጃቤት አስታወቀ ።</description>
            <link>http://www.waltainfo.com/AmNews/2006/Oct/09Oct06/19031.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">469EB9FE-57E5-11DB-B1BB-000393197FB0-420-000000E025E48595-FFA</guid>
            <pubDate>Mon, 09 Oct 2006 18:27:23 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>አፍሪካዊያን አካል ጉዳተኞች በሁሉም የስፖርት ዘርፎች እያደረጉት ያሉት ተሳትፎ እያደገ መምጣቱ ተገለፀ</title>
            <description>አፍሪካዊያን አካል ጉዳተኞች በሁሉም የስፖርት ዘርፎች እያደረጉት ያሉት ተሳትፎ እያደገ መምጣቱ ተገለፀ&lt;br&gt;&lt;br&gt;
አዲሰ አበባ መስከረም 29/1999/ዋኢማ /አፍሪካዊያን የአካል ጉዳተኞች በአህጉራቸውና በዓለም አቀፍ ደረጃ በሁሉም የስፖርት ዘርፎች እያደረጉት ያለው ተሳትፎ እድገት እያሳየ መምጣቱን የወጣቶችና ስፖርት ጉዳይ ሚኒስቴር ገለፀ።</description>
            <link>http://www.waltainfo.com/AmNews/2006/Oct/09Oct06/19059.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">385D3BD6-57E5-11DB-B1BB-000393197FB0-420-000000DFF68A7771-FFA</guid>
            <pubDate>Mon, 09 Oct 2006 18:26:57 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>የህዝብ ተወካዮችና የፌዴሬሽን ምክር ቤቶች ሶስተኛ ዘመን 2ኛ ዓመት ስራቸውን ዛሬ በይፋ ጀመሩ</title>
            <description>የህዝብ ተወካዮችና የፌዴሬሽን ምክር ቤቶች ሶስተኛ ዘመን 2ኛ ዓመት ስራቸውን ዛሬ በይፋ ጀመሩ&lt;br&gt;&lt;br&gt;
አዲስ አበባ መስከረም 29/1999/ዋኢማ/ የህዝብ ተወካዮችና የፌዴሬሽን ምክር ቤቶች በተያዘው ዓመት በሀገሪቱ የመድብለ ፓርቲ ስርዓትን ለማስፈንና ፈጣን ልማትና መልካም አስተዳደርን ለማረጋገጥ የሚያወጧቸውን ልዩ ልዩ አዋጆችንና ህጎችን ተግባራዊ ማድረግ እንደሚገባ ፕሬዚደንት ግርማ ወልደጊዮርጊስ አስገነዘቡ። የህዝብ ተወካዮችና የፌዴሬሽን ምክር ቤቶች ሶስተኛ ዘመን 2ኛ ዓመት ስራቸውን ዛሬ በይፋ ጀምረዋል።</description>
            <link>http://www.waltainfo.com/AmNews/2006/Oct/09Oct06/19060.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">2D870EC0-57E5-11DB-B1BB-000393197FB0-420-000000DFD28BD90A-FFA</guid>
            <pubDate>Mon, 09 Oct 2006 18:26:33 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>ከቀረጥ ነጻ ገብተው ወደ ሦስተኛ ወገን የተላለፉ ተሽከርካሪዎችን ሕጋዊ የማድረጊያው የጊዜ ገደብ ተራዘመ</title>
            <description>ከቀረጥ ነጻ ገብተው ወደ ሦስተኛ ወገን የተላለፉ ተሽከርካሪዎችን ሕጋዊ የማድረጊያው የጊዜ ገደብ ተራዘመ&lt;br&gt;&lt;br&gt;
አዲስ አበባ, ጥቅምት 25 ቀን 1999 - የኢትዮጵያ ጉምሩክ ባለሥልጣን ከቀረጥ ነጻ ገብተው ወደ ሦስተኛ ወገን የተላለፉ ተሽከርካሪዎችን ሕጋዊ ለማድረግ የተላለፈውን የጊዜ ገደብ አራዘመ፡፡ የሕገወጥ ዕቃዎች አሻሻጥ፣ አያያዝና የወረታ ክፍያዎችን ለመወሰን የሚያስችል መመሪያ ወጥቷል፡፡</description>
            <link>http://www.waltainfo.com/AmNews/2006/Oct/05Oct06/18920.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">88365F42-54C9-11DB-A3FC-000393197FB0-2313-000003C71FAB1CEE-FFA</guid>
            <pubDate>Thu, 05 Oct 2006 19:31:14 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>በዞኑ የዕጣን አምራች ማሕበራት የካፒታል መጠን 33 ሚሊየን ብር መድረሱ ተገለጸ</title>
            <description>በዞኑ የዕጣን አምራች ማሕበራት የካፒታል መጠን 33 ሚሊየን ብር መድረሱ ተገለጸ&lt;br&gt;&lt;br&gt;
አክሱም መስከረም 25/1999 /ዋኢማ/ በትግራይ ሰሜናዊ ምዕራብ ዞን አምስት ወረዳዎች በዕጣን ማምረት የተሰማሩ 23 ማሕበራት ምርቶቻቸውን ለማዕከላዊ ገበያ በማቅረብ ካፒታላቸውን ወደ 33 ሚሊየን ብር ማሳደጋቸውን የየወረዳዎቹ እርሻና ገጠር ልማት ጽህፈት ቤቶች አስታወቁ።</description>
            <link>http://www.waltainfo.com/AmNews/2006/Oct/05Oct06/18889.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">7E17E8B8-54C9-11DB-A3FC-000393197FB0-2313-000003C6FE0EB450-FFA</guid>
            <pubDate>Thu, 05 Oct 2006 19:31:30 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>ቢሮው የአርብቶ አደሮችን ህይወት ለመለወጥ በመሰረተ ልማት አግልግሎቶች ትኩረት እንደሚሰጥ ገለፀ</title>
            <description>ቢሮው የአርብቶ አደሮችን ህይወት ለመለወጥ በመሰረተ ልማት አግልግሎቶች ትኩረት እንደሚሰጥ ገለፀ&lt;br&gt;&lt;br&gt;
ጅጅጋ መስከረም 25/1999/ዋኢማ/ የሶማሌ ክልል አርብቶ አደሮች ልማት ማስተባበሪያ ቢሮ የአርብቶ አደሮችን ህይወት ለመለወጥ የሚያስችሉ የመሰረተ ልማት አገልግሎቶችን ለማሟላት ቅድሚያ ትኩረት መስጠቱን ገለፀ።</description>
            <link>http://www.waltainfo.com/AmNews/2006/Oct/05Oct06/18907.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">77F2166C-54C9-11DB-A3FC-000393197FB0-2313-000003C6E9A32A3D-FFA</guid>
            <pubDate>Thu, 05 Oct 2006 19:31:44 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>የአደረጃጀትና የሰው ሀይል ችግሮቹ የፍትህ ተቋማቱን አቅም ጠንካራ እንዳይሆን ማድረጋቸው ተገለፀ</title>
            <description>የአደረጃጀትና የሰው ሀይል ችግሮቹ የፍትህ ተቋማቱን አቅም ጠንካራ እንዳይሆን ማድረጋቸው ተገለፀ&lt;br&gt;&lt;br&gt;
አዲስ አበባ መስከረም 25/1999/ዋኢማ/ በፍትህ ስርዕቱ አሰራር ላይ የሚታዩ የአደረጃጀትና የሰው ሀይል ችግሮች የፍትህ ተቋማቱ ዓቅም የተፈለገውን ያህል ጠንካራ እንዳይሆን አድርገውት መቆየታቸውን የፍትህ ሚኒስትሩ ገለጹ።</description>
            <link>http://www.waltainfo.com/AmNews/2006/Oct/05Oct06/18901.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">6A82CF4A-54C9-11DB-A3FC-000393197FB0-2313-000003C6BD0355A9-FFA</guid>
            <pubDate>Thu, 05 Oct 2006 19:32:01 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>የፓራሊምፒክ ኮሚቴ ለመላው አፍሪካ ጨዋታዎችና ለቤጂንግ ኦሎምፒክ የሚቀርቡ ስፖርተኞችን በማሰልጠን ላይ ነው</title>
            <description>የፓራሊምፒክ ኮሚቴ ለመላው አፍሪካ ጨዋታዎችና ለቤጂንግ ኦሎምፒክ የሚቀርቡ ስፖርተኞችን በማሰልጠን ላይ ነው&lt;br&gt;&lt;br&gt;
አዲስ አበባ መስከረም 25/1999/ዋኢማ/ የኢትዮጵያ ፓራሊምፒክ ኮሚቴ በ2007 አልጀርስ ለሚካሄደው የመላው አፍሪካ ጨዋታዎችና ለቤጂንግ ኦሎምፒክ ኢትዮጵያን የሚወክሉ 44 ስፖርተኞችን መልምሎ ስልጠና እየሰጠ መሆኑን አስታወቀ።</description>
            <link>http://www.waltainfo.com/AmNews/2006/Oct/05Oct06/18893.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">629BFC38-54C9-11DB-A3FC-000393197FB0-2313-000003C6A2C45E27-FFA</guid>
            <pubDate>Thu, 05 Oct 2006 19:32:18 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>የምዕተ ዓመቱን ግብ ለማሳካትና ድህነትን ለማጥፋት ለከርሰ ምድር ውሃ ትኩረት መስጠት እንደሚገባ ተገለጸ</title>
            <description>የምዕተ ዓመቱን ግብ ለማሳካትና ድህነትን ለማጥፋት ለከርሰ ምድር ውሃ ትኩረት መስጠት እንደሚገባ ተገለጸ&lt;br&gt;&lt;br&gt;
አዲስ አበባ መስከረም 25/1/1999/ዋኢማ/ የምዕተ ዓመቱን ግብ ለማሳካትና ድህነትን ለማጥፋት ሀገሪቱ ያላትን የከርሰ ምድር ውሃ ክምችት ለተለያዩ ግልጋሎቶች የሚውልበት መንገድ ማመቻቸት እንደሚገባ የውሃ ሃብት ልማት ሚኒስትር አስገነዘቡ። መንግስት ብሔራዊ የውሃ ፖሊሲ ነድፎ በመንቀሳቀስ ላይ እንደሆነም ገልጸዋል።</description>
            <link>http://www.waltainfo.com/AmNews/2006/Oct/05Oct06/18910.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">58E7172E-54C9-11DB-A3FC-000393197FB0-2313-000003C682869C39-FFA</guid>
            <pubDate>Thu, 05 Oct 2006 19:32:30 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>የፌደራል ጉዳዮች ሚኒስትር ሲራጅ ፌጌሳ በስዋዚላንድ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ሞት የተሰማቸውን ሃዘን ገለጹ</title>
            <description>የፌደራል ጉዳዮች ሚኒስትር ሲራጅ ፌጌሳ በስዋዚላንድ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ሞት የተሰማቸውን ሃዘን ገለጹ&lt;br&gt;&lt;br&gt;
አዲስ አበባ መስከረም 25/1999/ዋኢማ/ የፌደራል ጉዳዮች ሚኒስትር ሲራጅ ፌጌሳ በስዋዚላንድ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አልበርት ሂሻኔ ሻባንጉ ሞት የተሰማቸውን ጥልቅ ሐዘን ገለጹ። ለስዋዚላንድ ህዝብና ለቤተሰቦቻቸውም መጽናናትን ተመኝተዋል።</description>
            <link>http://www.waltainfo.com/AmNews/2006/Oct/05Oct06/18908.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">45FE7DEC-54C9-11DB-A3FC-000393197FB0-2313-000003C643B83592-FFA</guid>
            <pubDate>Thu, 05 Oct 2006 19:32:39 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>የዓለም ማህበረሰብ በሶማሊያ ጉዳይ ላይ ጣልቃ ካልገባ በአህጉሩ ከፍተኛ ትርምስ ሊፈጠር እንደሚችል ተገለጸ</title>
            <description>የዓለም ማህበረሰብ በሶማሊያ ጉዳይ ላይ ጣልቃ ካልገባ በአህጉሩ ከፍተኛ ትርምስ ሊፈጠር እንደሚችል ተገለጸ&lt;br&gt;&lt;br&gt;
አዲስ አበባ መስከረም 25/1999/ዋኢማ/ የዓለም ማህበረሰብ በሶማሊያ ጉዳይ ላይ ጣልቃ ካልገባ በእስላማዊ ፍርድ ቤቶች ህብረት ጥላ ስር ተከልሎ የሚገኘው አሸባሪ ኃይል መስፋፋት ለቀጣናውና ለአህጉሩ ሠላም መናጋት ከፍተኛ ጠንቅ እንደሚሆን በሶማሊያ ወቅታዊ ሁኔታ ላይ ጥናት ያካሄዱ አንድ ምሁር ገለጹ።</description>
            <link>http://www.waltainfo.com/AmNews/2006/Oct/05Oct06/18885.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">38E50EBC-54C9-11DB-A3FC-000393197FB0-2313-000003C6183588AE-FFA</guid>
            <pubDate>Thu, 05 Oct 2006 19:32:47 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>በጋምቤላ ክልል ፈቃድ ከወሰዱት26 ባለሀብቶች መካከል ዘጠኙ ማምረት መጀመራቸው ተገለፀ</title>
            <description>በጋምቤላ ክልል ፈቃድ ከወሰዱት26 ባለሀብቶች መካከል ዘጠኙ ማምረት መጀመራቸው ተገለፀ&lt;br&gt;&lt;br&gt;
ጋምቤላ መስከረም 25/1999/ዋኢማ/በጋምቤላ ክልል 100 ሚሊየን ብር ካፒታል አስመዝግበው ፈቃድ ከወሰዱ 26 ባለሃብቶች መካከል ዘጠኙ ማምረት መጀመራቸውን የክልሉ ኢንቨስትመንት ኤጀንሲ ገለፀ፡፡</description>
            <link>http://www.waltainfo.com/AmNews/2006/Oct/05Oct06/18883.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">2BF78EE4-54C9-11DB-A3FC-000393197FB0-2313-000003C5ED44CB1B-FFA</guid>
            <pubDate>Thu, 05 Oct 2006 19:33:00 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>በሃገራችን ለመጀመሪያ ጊዜ በቤተሙከራ ዕገዛ የተወለደች ህጻን በመልካም ጤንነት ላይ እንደምትገኝ ተገለጸ</title>
            <description>በሃገራችን ለመጀመሪያ ጊዜ በቤተሙከራ ዕገዛ የተወለደች ህጻን በመልካም ጤንነት ላይ እንደምትገኝ ተገለጸ&lt;br&gt;&lt;br&gt;
አዲስአበባ መስከረም 25/1999/ዋኢማ/ በተለያየ ምክንያት መውለድ ያልቻሉ ባለትዳሮችን በህክምና ዕርዳታ እንዲወልዱ ለማስቻል በሃገራችን ለመጀመሪያ ጊዜ በተደረገው ሙከራ በተያዘው ወር የመጀመሪያ ሳምንት የተወለደች ህጻን በመልካም ጤንነት ላይ እንደምትገኝ የቤተል ቲቺንግ ሆስፒታል ማኔጂንግ ዳይሬክተር አስታወቁ። የህጻኗ እናትም ልጅ ለማግኘት እየፈለጉ መውለድ ያልቻሉ ቤተሰቦች ህክምናውን ቢሞክሩት ምኞታቸው ሊሳካላቸው እንደሚችል መክረዋል።</description>
            <link>http://www.waltainfo.com/AmNews/2006/Oct/05Oct06/18905.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">242D2AA0-54C9-11DB-A3FC-000393197FB0-2313-000003C5D364468F-FFA</guid>
            <pubDate>Thu, 05 Oct 2006 19:33:59 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>የአውሮፓ ኢንቨስትመንት ባንክ ለንግዱ ማህበረሰብ ስምንት ሚሊየን ዩሮ ብድር እንደሚሰጥ አስታወቀ</title>
            <description>የአውሮፓ ኢንቨስትመንት ባንክ ለንግዱ ማህበረሰብ ስምንት ሚሊየን ዩሮ ብድር እንደሚሰጥ አስታወቀ&lt;br&gt;&lt;br&gt;
አዲስ አበባ መስከረም 25 /1999/ዋኢማ/ የአውሮፓ ኢንቨስትመንት ባንክ የአገራችን የንግዱን ማህበረሰብ የንግድና የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ ለማጠናከር የስምንት ሚሊየን ዩሮ ብድር እንደሚሰጥ አስታወቀ፡፡</description>
            <link>http://www.waltainfo.com/AmNews/2006/Oct/05Oct06/18886.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">1A7ACED2-54C9-11DB-A3FC-000393197FB0-2313-000003C5B32EF1AB-FFA</guid>
            <pubDate>Thu, 05 Oct 2006 19:34:12 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>ኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባል ለመሆን የጀመረችው እንቀስቃሴ ፈጣን ዕድገት ለማምጣት እንደሚረዳት ተገለጸ</title>
            <description>ኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባል ለመሆን የጀመረችው እንቀስቃሴ ፈጣን ዕድገት ለማምጣት እንደሚረዳት ተገለጸ&lt;br&gt;&lt;br&gt;
ባህርዳር መስከረም 25/1999/ዋኢማ/ ኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባል ለመሆን የጀመረችው እንቀስቃሴ በሀገሪቱ ፈጣን ዕድገት ለማምጣት ከነደፈችው የዕድገት መርሃ ግብር እንደ አንድ አጀንዳ ከተወስደው ይበልጥ ተጠቃሚ እንደምትሆን የአሜሪካን ኤምባሲ የልዑካን ቡድን ገለጸ። ሀገሪቱ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል እንደትሆን ባቀረበችው ጥያቄ መሰረት የወጪ ንግድ ስርዓቷን የሚያሳይ ሰነድ ተዘጋጅቶ ለሚኒስትሮች ምክር ቤት መቅረቡን የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ገልጿል።</description>
            <link>http://www.waltainfo.com/AmNews/2006/Oct/05Oct06/18915.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">10B34A33-54C9-11DB-A3FC-000393197FB0-2313-000003C592B35446-FFA</guid>
            <pubDate>Thu, 05 Oct 2006 19:34:21 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>ለብዝሀ ሕይወት ጥበቃ ኅብረተሰቡን ማሳተፍ እንደሚገባ ፕሬዚዳንት ግርማ አሳሰቡ</title>
            <description>ለብዝሀ ሕይወት ጥበቃ ኅብረተሰቡን ማሳተፍ እንደሚገባ ፕሬዚዳንት ግርማ አሳሰቡ&lt;br&gt;&lt;br&gt;
አዲስ አበባ መስከረም 24/1999 - የሀገሪቱን የብዝሀ ሕይወት ሀብት ለመጠበቅ እየተደረገ ባለው ጥረት ኅብረተሰቡን ማሳተፍ እንደ ሚገባ ፕሬዚዳንት ግርማ ወልደጊዮርጊስ አሳሰቡ፡፡ትናንት የብዝሀ ሕይወት ጥበቃና ድህነት ቅነሳ በሚል መርህ በግዮን ሆቴል የተጀመረውን ዓውደጥናት በንግግር የከፈቱት ፕሬዚዳንት ግርማ እንደገለጹት፤ መንግሥት ብዝሀ ሕይወትን ለመጠበቅ የሚያስችሉ በርካታ ተግባራትን ያከናወነ ቢሆንም የበለጠ ውጤታማ ለመሆን ኅብረተሰቡን ማሳተፍ ይገባል፡፡</description>
            <link>http://www.waltainfo.com/AmNews/2006/Oct/04Oct06/18880.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">5A07305A-53D5-11DB-989D-000393197FB0-407-0000009C0ABEE191-FFA</guid>
            <pubDate>Wed, 04 Oct 2006 14:23:35 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>አምባሳደር ሱሌይማን ደደፎ የሹመት ደብዳቤያቸውን ለናይጄሪያው ፕሬዚዳንት አቀረቡ</title>
            <description>አምባሳደር ሱሌይማን ደደፎ የሹመት ደብዳቤያቸውን ለናይጄሪያው ፕሬዚዳንት አቀረቡ&lt;br&gt;&lt;br&gt;
አዲስ አበባ መስከረም 24/1999 - በናይጄሪያ የኢትዮጵያ መንግሥት ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደርና ልዩ መልእክተኛ ሆነው የተሾሙት አምባሳደር ሱሌይማን ደደፎ የሹመት ደብዳቤአቸውን ለናይጄሪያው ፕሬዚዳንት ኦሊሴጎን ኦባሳንጆ ሰሞኑን ማቅረባቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡</description>
            <link>http://www.waltainfo.com/AmNews/2006/Oct/04Oct06/18879.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">3288BB28-53D5-11DB-989D-000393197FB0-407-0000009B8790459F-FFA</guid>
            <pubDate>Wed, 04 Oct 2006 14:24:24 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>ኢትዮጵያ በሶማሊያ ሰላም እንዲሰፍን የምታደርገውን ጥረት የምታጠናክር መሆኗን ጠቅላይ ሚኒስትሩ አስታወቁ</title>
            <description>ኢትዮጵያ በሶማሊያ ሰላም እንዲሰፍን የምታደርገውን ጥረት የምታጠናክር መሆኗን ጠቅላይ ሚኒስትሩ አስታወቁ -&lt;br&gt;&lt;br&gt;
አዲስ አበባ መስከረም 24/1999 - ኢትዮጵያ በሶማሊያ የተረጋጋና ምቹ የሆነ ሰላምና ፀጥታ እንዲሰፍን አሁንም ሆነ ወደፊት የምታደርገውን ጥረት አጠናክራ እንደ ምትቀጥል ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ አስታወቁ፡፡</description>
            <link>http://www.waltainfo.com/AmNews/2006/Oct/04Oct06/18878.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">02BAFE7D-53D5-11DB-989D-000393197FB0-407-0000009AE8C7BAC6-FFA</guid>
            <pubDate>Wed, 04 Oct 2006 14:25:43 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>በረሃማነትን ለመቀነስ የተጠናከረ አከባቢን የመከላከል ስራ መስራት እንደሚያስፈልግ ተገለጸ</title>
            <description>በረሃማነትን ለመቀነስ የተጠናከረ አከባቢን የመከላከል ስራ መስራት እንደሚያስፈልግ ተገለጸ&lt;br&gt;&lt;br&gt;
ጅጅጋ መስከረም 24/1999/ዋኢማ/ የበረሃማነት መስፋፋት በዝናብ አጠር አከባቢዎች የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እየተደረገ ያለውን ጥረት እንዳያደናቅፈው የተጠናከረ አከባቢን የመከላከል ስራ መስራት እንደሚያስፈልግ ተገለጸ።</description>
            <link>http://www.waltainfo.com/AmNews/2006/Oct/04Oct06/18869.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">EFFD33EC-53D4-11DB-989D-000393197FB0-407-0000009AAA878824-FFA</guid>
            <pubDate>Wed, 04 Oct 2006 14:26:03 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>ድርጅቱ ለአማራጭ መሰረታዊ ትምህርት ማጠናከሪያ 195 ሺ ብር የሚያወጡ ቁሳቁስ በዕርዳታ ሰጠ</title>
            <description>ድርጅቱ ለአማራጭ መሰረታዊ ትምህርት ማጠናከሪያ 195 ሺ ብር የሚያወጡ ቁሳቁስ በዕርዳታ ሰጠ&lt;br&gt;&lt;br&gt;
አሶሳ መስከረም 24/1999/ዋኢማ/ አክሽን ኤድ ኢትዮጵያ የአሶሳ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ለአማራጭ መሰረታዊ ትምህርት ማጠናከሪያ የሚረዱ ግምታቸው 195 ሺ ብር የሆኑ የተለያዩ ቁሳቁስ ለክልሉ ትምህርት ቢሮ በዕርዳታ ሰጠ።</description>
            <link>http://www.waltainfo.com/AmNews/2006/Oct/04Oct06/18859.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">E2899E24-53D4-11DB-989D-000393197FB0-407-0000009A7DD965F3-FFA</guid>
            <pubDate>Wed, 04 Oct 2006 14:27:40 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>ባለፈው ዓመት ከ15 ሺ በላይ የቤተሰብ መሪ አርሶ አደሮች የተሻለ ለምነት ባላቸው አካባቢዎች መስፈራቸው ተገለጸ</title>
            <description>ባለፈው ዓመት ከ15 ሺ በላይ የቤተሰብ መሪ አርሶ አደሮች የተሻለ ለምነት ባላቸው አካባቢዎች መስፈራቸው ተገለጸ&lt;br&gt;&lt;br&gt;
አዲስ አበባ መስከረም 24/1999/ዋኢማ/ በሶስት ክልሎች ለአራተኛ ጊዜ በተካሄደው የሰፈራ ፕሮግራም 15 ሺ 546 የቤተሰብ መሪ አርሶአደሮችን የተሻለ ለምነት ወዳላቸው አካባቢዎች ማስፈር መቻሉን በግብርናና ገጠር ልማት ሚኒስቴር የምግብ ዋስትና ማስተባበሪያ ቢሮ አስታወቀ። ባለፉት ሶስት ዙሮች ከሰፈሩት 549 ሺ 545 የቤተሰብ መሪ አርሶ አደሮች ውስጥ 132 ሺ 496 የሚሆኑት በምግብ ራሳቸውን እንደቻሉ ተረጋግጧል።</description>
            <link>http://www.waltainfo.com/AmNews/2006/Oct/04Oct06/18857.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">D48D878B-53D4-11DB-989D-000393197FB0-407-0000009A4F65E0AD-FFA</guid>
            <pubDate>Wed, 04 Oct 2006 14:28:20 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>በትግራይ ፈጣን የኢንቨስትመንት ፈቃድ አሰጣጥ ሥርዓት መመቻቸቱ ተገለጸ</title>
            <description>በትግራይ ፈጣን የኢንቨስትመንት ፈቃድ አሰጣጥ ሥርዓት መመቻቸቱ ተገለጸ&lt;br&gt;&lt;br&gt;
መቀሌ መስከረም 24 /1999/ዋኢማ/ በትግራይ ክልል ለባለሃብቶች ፈጣን የኢንቨስትመንት ፈቃድ አሰጣጥ ሥርዓት በመዘርጋቱ በክልሉ ልማት የሚሳተፉ ባለሃብቶች ቁጥር እየጨመረ መምጣቱን የክልሉ ኢንቨስትመንት ጽሕፈት ቤት አስታወቀ።</description>
            <link>http://www.waltainfo.com/AmNews/2006/Oct/04Oct06/18858.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">C5966D11-53D4-11DB-989D-000393197FB0-407-0000009A1DB09875-FFA</guid>
            <pubDate>Wed, 04 Oct 2006 14:28:43 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>በትግራይ 10ኛ ክፍል ከተፈተኑት ተማሪዎች ከግማሽ በላይ የሚሆኑት ሁለትና ከዛ በላይ ነጥብ አገኙ</title>
            <description>በትግራይ 10ኛ ክፍል ከተፈተኑት ተማሪዎች ከግማሽ በላይ የሚሆኑት ሁለትና ከዛ በላይ ነጥብ አገኙ&lt;br&gt;&lt;br&gt;
መቀሌ መስከረም 24/1999/ዋኢማ/ በትግራይ ክልል በ1998 ዓ ም የ10ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ከወሰዱት ተማሪዎች ውስጥ ከግማሽ በላይ የሚሆኑት ሁለት ነጥብና ከዛ በላይ ማግኘታቸው ተገለጸ ።</description>
            <link>http://www.waltainfo.com/AmNews/2006/Oct/04Oct06/18874.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">B4B6C658-53D4-11DB-989D-000393197FB0-407-00000099E5A48D4A-FFA</guid>
            <pubDate>Wed, 04 Oct 2006 14:30:31 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>የክልሉን ልማት ለማፋጠን የሚያስችል የህዝብ ግንኙነት ሥራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ተባለ</title>
            <description>የክልሉን ልማት ለማፋጠን የሚያስችል የህዝብ ግንኙነት ሥራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ተባለ&lt;br&gt;&lt;br&gt;
ባሕርዳር መስከረም 24/1999/ዋኢማ/ በአማራ ክልል የተጀመረውን ልማት ለማፋጠን በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገራት ለሚገኙ ኢትዮጵያዊያን በቂ መረጃ በመስጠት የልማቱ ግንባር ቀደም ተሳታፊ እንዲሆኑ ለማስቻል የተጀመረው የህዝብ ግነኙነት ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ገለፁ።</description>
            <link>http://www.waltainfo.com/AmNews/2006/Oct/04Oct06/18849.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">9F990E3E-53D4-11DB-989D-000393197FB0-407-000000999F8110BD-FFA</guid>
            <pubDate>Wed, 04 Oct 2006 14:32:56 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>የአርባ ምንጭ አዞ ዕርባታ ጣቢያ ባለፈው የበጀት ዓመት ከሶስት ሺ በላይ የአዞ ቆዳ ለዓለም ገበያ ማቅረቡን አስታወቀ</title>
            <description>የአርባ ምንጭ አዞ ዕርባታ ጣቢያ ባለፈው የበጀት ዓመት ከሶስት ሺ በላይ የአዞ ቆዳ ለዓለም ገበያ ማቅረቡን አስታወቀ&lt;br&gt;&lt;br&gt;
አርባ ምንጭ መስከረም 24/1998/ዋኢማ/ የአርባ ምንጭ አዞ ዕርባታ ጣቢያ ባለፈው የበጀት ዓመት ከሶስት ሺ በላይ የአዞ ቆዳ ለዓለም ገበያ ማቅረቡን አስታወቀ። በውጭው ማህበረሰብ ዘንድ በምግብነት ተፈላጊነቱ እየጨመረ የመጣውን የአዞ ሥጋ ለገበያ ለማቅረብና የሰጎን ዕርባታ ለመጀመር ማቀዱንም ገልጿል።</description>
            <link>http://www.waltainfo.com/AmNews/2006/Oct/04Oct06/18848.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">926EF5B1-53D4-11DB-989D-000393197FB0-407-0000009973C70CC4-FFA</guid>
            <pubDate>Wed, 04 Oct 2006 14:34:00 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>የውሀ ሀብት ልማት ሚኒስቴር የንጹህ የመጠጥ ውኃና የሳንቴሽን ሽፋንን በሁሉም የገጠር አካባቢዎች ለማዳረስ የሚያስችለው ፕሮግራም ስራ ላይ ማዋሉን አስታወቀ</title>
            <description>የውሀ ሀብት ልማት ሚኒስቴር የንጹህ የመጠጥ ውኃና የሳንቴሽን ሽፋንን በሁሉም የገጠር አካባቢዎች ለማዳረስ የሚያስችለው ፕሮግራም ስራ ላይ ማዋሉን አስታወቀ&lt;br&gt;&lt;br&gt;
አዲስ አበባ መስከረም 24/1999/ዋኢማ/ የውሀ ሀብት ልማት ሚኒስቴር የንጹህ የመጠጥ ውኃና የሳንቴሽን ሽፋንን በሁሉም የገጠር አካባቢዎች በሰባት ዓመታት ጊዜ ውስጥ ለማዳረስ የሚያስችል የዩኒቨርሳል አክሰስ ፕሮግራም መጀመሩን አስታወቀ። ለፕሮግራሙ ማስፈፀሚያ ከ10 ቢሊየን ብር በላይ እንደሚያስፈልግ ተገለፀ።</description>
            <link>http://www.waltainfo.com/AmNews/2006/Oct/04Oct06/18846.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">7B3B92FE-53D4-11DB-989D-000393197FB0-407-0000009926B6F1A3-FFA</guid>
            <pubDate>Wed, 04 Oct 2006 14:35:05 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>ኢንስቲትዩቱ ከ5ሺ ለሚበልጡ የስራ አስፈጻሚ አካላትየአቅም ግንባታ ሥልጠና ሊሰጥ ነው</title>
            <description>ኢንስቲትዩቱ ከ5ሺ ለሚበልጡ የስራ አስፈጻሚ አካላትየአቅም ግንባታ ሥልጠና ሊሰጥ ነው&lt;br&gt;&lt;br&gt;
ባህር ዳር መስከረም 24/1999/ዋኢማ/የአማራ ክልል ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት በተያዘው የበጀት አመት ከ5 ሺ500 ለሚበልጡ የስራ አስፈጻሚ አካላትን የአቅም ግንባታ ሥልጠና ለመስጠት መዘጋጀቱን አስታወቀ።</description>
            <link>http://www.waltainfo.com/AmNews/2006/Oct/04Oct06/18847.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">824F5B19-53D4-11DB-989D-000393197FB0-407-000000993E38EB62-FFA</guid>
            <pubDate>Wed, 04 Oct 2006 14:34:26 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>ኮርፖሬሽኑ 18 ከተሞችን የዲጅታል ስልክ አገልግሎት ተጠቃሚ ማድረጉን አስታወቀ</title>
            <description>ኮርፖሬሽኑ 18 ከተሞችን የዲጅታል ስልክ አገልግሎት ተጠቃሚ ማድረጉን አስታወቀ&lt;br&gt;&lt;br&gt;
ሐረር መስከረም 24 /1999/ /ዋኢማ/ የኢትዮጵያ ቴሌኮሙኒኬሽን ኮርፖሬሽን ከ65 ነጥብ4 ሚሊየን ብር በሚበልጥ ወጪ በምስራቅ ኢትዮጵያ የሚገኙ 18 ከተሞችን ዘመናዊ የዲጂታል አውቶማቲክ ስልክ ተጠቃሚ ማድረጉን አስታወቀ።660 የገጠር ቀበሌ ገበሬ ማህበራት የሽቦ አልባ ስልክ ተጠቃሚ መሆናቸውንም ገለፀ።</description>
            <link>http://www.waltainfo.com/AmNews/2006/Oct/04Oct06/18855.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">69072F64-53D4-11DB-989D-000393197FB0-407-00000098EA3F2026-FFA</guid>
            <pubDate>Wed, 04 Oct 2006 14:36:37 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>ብሔራዊ ቡድኑ ከናሚቢያ ጋር ላለበት ጨዋታ የፊታችን ሐሙስ ወደ ዊንድሆክ ሊጓዛ ነው</title>
            <description>ብሔራዊ ቡድኑ ከናሚቢያ ጋር ላለበት ጨዋታ የፊታችን ሐሙስ ወደ ዊንድሆክ ሊጓዛ ነው&lt;br&gt;&lt;br&gt;
አዲስ አበባ መስከረም 23/1999/ዋኢማ/ በ2008 በጋና በሚካሄደው 26ኛ የአፍሪካ ዋንጫ ላይ ለመሳተፍ የማጣሪያ ጨዋታዎች በማድረግ ላይ የሚገኘው የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን የፊታችን ዕሁድ ከናሚቢያ ጋር ላለበት ጨዋታ በቂ ዝግጅት ማድረጉን አሰልጣኝ ስዩም አባተ ገለፁ። ቡድኑ የፊታችን ሐሙስ ወደ ዊንድሆክ ይጓዛል።</description>
            <link>http://www.waltainfo.com/AmNews/2006/Oct/03Oct06/18823.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">8F18DECE-534D-11DB-9535-000393197FB0-646-0000003D1466F72D-FFA</guid>
            <pubDate>Tue, 03 Oct 2006 22:11:28 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>በቅጅ መብት ጥሰትና ዘረፋ ላይ የተሰማሩ አካላትን ለመከላከል የወጣውን ህግ ማስፈጸም እንደሚገባ ተገለፀ</title>
            <description>በቅጅ መብት ጥሰትና ዘረፋ ላይ የተሰማሩ አካላትን ለመከላከል የወጣውን ህግ ማስፈጸም እንደሚገባ ተገለፀ&lt;br&gt;&lt;br&gt;
አዲስ አበባ መስከረም 23/1999/ዋኢማ/ በቅጅ መብት ጥሰትና ዘረፋ ላይ የተሰማሩ ህገ ወጥ አካላትን ህግ ፊት ለማቅረብ የወጣውን ህግ ለመተግበር ህግ ተርጓሚውና አስፈጻሚው አካል ተቀናጅቶ መንቀሳቀስ እንደሚገባው የኢትዮጵያ የአዕምራዊ ንብረት ጽህፈት ቤት ገለፀ።.</description>
            <link>http://www.waltainfo.com/AmNews/2006/Oct/03Oct06/18834.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">835AE7A2-534D-11DB-9535-000393197FB0-646-0000003CED666B06-FFA</guid>
            <pubDate>Tue, 03 Oct 2006 22:10:51 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>ተቋሙ 93 በምርምር የተሻሻሉ የሰብል፣ የመኖ፣ የጓሮ አትክልትና የፍራፍሬ ዝሪያዎችን ሰበሰበ</title>
            <description>ተቋሙ 93 በምርምር የተሻሻሉ የሰብል፣ የመኖ፣ የጓሮ አትክልትና የፍራፍሬ ዝሪያዎችን ሰበሰበ&lt;br&gt;&lt;br&gt;
ጅጅጋ መስከረም 23/1999/ዋኢማ/ የሶማሌ ክልል አርብቶ አደርና ከፊል አርብቶ አደር ምርምር ተቋም 93 የተሻሻሉ የሰብል፣ የመኖ፣ የጓሮ አትክልትና የፍራፍሬ ዝሪያዎችን ከአከባቢው የአየር ፀባይ ጋር ለማላመድ ከውጭና ከአገር ውስጥ የምርምር ማዕከላት መሰብሰቡን ገለፀ፤ ለቀጣይ የምርምር ስራዎች መሠረት የሚጥሉ 18 የቅኝት ጥናቶች የሚካሄዱ መሆናቸውንም አስታወቋል።</description>
            <link>http://www.waltainfo.com/AmNews/2006/Oct/03Oct06/18832.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">73309CDC-534D-11DB-9535-000393197FB0-646-0000003CB7B4C122-FFA</guid>
            <pubDate>Tue, 03 Oct 2006 22:10:31 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>አርቲሚዝያ የተባለ ለመድሃኒትነት የሚያገለግል ተክል በመቀሌ በችግኝ ማፊያዎች እየተሞከረ መሆኑ ተገለፀ</title>
            <description>አርቲሚዝያ የተባለ ለመድሃኒትነት የሚያገለግል ተክል በመቀሌ በችግኝ ማፊያዎች እየተሞከረ መሆኑ ተገለፀ&lt;br&gt;&lt;br&gt;
መቀሌ መስከረም 23/1999/ዋኢማ/ በመድሃኒት ፋብሪካዎች ለመድሃኒትነት ቅመማ የሚያገለግል አርቲሚዚያ የተባለ ተክል በመቀሌ አከባቢ በሚገኙ የችግኝ ማፊያ ጣቢያዎች እየተሞከረ መሆኑን የትግራይ ክልል ግብርናና ገጠር ልማት ቢሮ አስታወቀ።</description>
            <link>http://www.waltainfo.com/AmNews/2006/Oct/03Oct06/18830.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">5F1474CA-534D-11DB-9535-000393197FB0-646-0000003C74E8C018-FFA</guid>
            <pubDate>Tue, 03 Oct 2006 22:10:04 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>ዩኒቨርስቲው የስኳር ድንችን ቅጠል ጠቀሜታ ለአርሶ አደሮች በማስተዋወቅ ላይ መሆኑን ገለፀ</title>
            <description>ዩኒቨርስቲው የስኳር ድንችን ቅጠል ጠቀሜታ ለአርሶ አደሮች በማስተዋወቅ ላይ መሆኑን ገለፀ&lt;br&gt;&lt;br&gt;
ሐረር መስከረም 23/ 1999/ ዋኢማ/ የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ስኳር ድንች ከሥሩ ይልቅ ቅጠሉ ከፍተኛ የምግብ ጠቀሜታ እንዳለው በመረጋገጡ ለአርሶ አደሮች በማስተዋወቅ ላይ መሆኑን አስታወቀ።በተያዘው የፈረንጆች ዓመት በምርምር ያገኘውን አዲስ የቦሎቄ ዝርያ ለአርሶ አደሮች ለማሰራጨት በማባዛት ላይ መሆኑንም ገለፀ።</description>
            <link>http://www.waltainfo.com/AmNews/2006/Oct/03Oct06/18818.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">46E47949-534D-11DB-9535-000393197FB0-646-0000003C24919DCB-FFA</guid>
            <pubDate>Tue, 03 Oct 2006 22:09:30 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>በባህርዳር የመኖሪያ ቤት እጥረትን ለማቃለል ለ3 ሺ 200 ነዋሪዎች የቤት መሥሪያ ቦታ ይሰጣል</title>
            <description>በባህርዳር የመኖሪያ ቤት እጥረትን ለማቃለል ለ3 ሺ 200 ነዋሪዎች የቤት መሥሪያ ቦታ ይሰጣል&lt;br&gt;&lt;br&gt;
ባሕር ዳር መስከረም 23/1999/ዋኢማ/ በባሕር ዳር ከተማ የሚታየውን የመኖሪያ ቤት እጥረት ለማቃለል በተያዘው የበጀት ዓመት ከ3 ሺ 200 ለሚበልጡ የከተማዋ ነዋሪዎች የመኖሪያ ቤት መሥሪያ ቦታ እንደሚሰጥ የከተማዋ ማስታወቂያ ጽሕፈት ቤት ገለፀ።የመኖሪያ ቦታዎችን በማስረከቡ ሂደት ከመሬታቸው ለሚፈናቀሉ አርሶ አደሮችና ባለይዞታዎች ከ47 ሚሊየን ብር በላይ የካሣ ክፍያ መዘጋጀቱንም አስታውቋል።</description>
            <link>http://www.waltainfo.com/AmNews/2006/Oct/03Oct06/18816.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">3550C240-534D-11DB-9535-000393197FB0-646-0000003BEA2F8549-FFA</guid>
            <pubDate>Tue, 03 Oct 2006 22:08:50 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>በደቡብ ክልል የመስኖ ተጠቃሚዎችን ቁጥር 80ሺ ለማድረስ የሚያስችል እንቅስቃሴ ተጀመረ</title>
            <description>በደቡብ ክልል የመስኖ ተጠቃሚዎችን ቁጥር 80ሺ ለማድረስ የሚያስችል እንቅስቃሴ ተጀመረ-&lt;br&gt;&lt;br&gt;
አዋሳ መስከረም 23/1999/ዋኢማ/ በደቡብ ክልል በቀጣዮቹ ሶስት ዓመታት የመስኖ ተጠቃሚዎችን ቁጥር ከ42 ሺ ወደ 80 ሺ ለማሳደግ የሚያስችል እንቅስቃሴ መጀመሩን የክልሉ ውሃ ሀብት ልማት ቢሮ አስታወቀ፤ለፕሮግራሙ ማስፈጸሚያ የ78 ሚሊየን ብር በጀት ተመድቧል።</description>
            <link>http://www.waltainfo.com/AmNews/2006/Oct/03Oct06/18815.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">23E7F7B8-534D-11DB-9535-000393197FB0-646-0000003BB05BE396-FFA</guid>
            <pubDate>Tue, 03 Oct 2006 22:08:20 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>በቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል የኅብረት ሥራ ማኅበራትን ለማጠመናከር 10 ሚሊየን ብር ተመደበ</title>
            <description>በቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል የኅብረት ሥራ ማኅበራትን ለማጠመናከር 10 ሚሊየን ብር ተመደበ&lt;br&gt;&lt;br&gt;
አሶሳ መስከረም 23/1999/በቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልል የተቋቋሙ 60 የገጠር አነስተኛ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ሕብረት ስራ ማህበራትን ለማጠናከር 10 ሚሊየን ብር መመደቡን የክልሉ የገጠር አነስተኛ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ማስፋፊያ ፕሮግራም አስታወቀ፡፡</description>
            <link>http://www.waltainfo.com/AmNews/2006/Oct/03Oct06/18808.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">1222A42A-534D-11DB-9535-000393197FB0-646-0000003B7554EAD8-FFA</guid>
            <pubDate>Tue, 03 Oct 2006 22:07:51 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>የአረጋውያንን ተሳትፎ ለማሳደግ የሚያስችሉ የአፈጻጸም መመሪያዎች እንደሚወጡ ተገለጸ</title>
            <description>የአረጋውያንን ተሳትፎ ለማሳደግ የሚያስችሉ የአፈጻጸም መመሪያዎች እንደሚወጡ ተገለጸ&lt;br&gt;&lt;br&gt;
አዲስ አበባ መስከረም 23/1999 ዋኢማ / በተያዘው የበጀት ዓመት የአረጋውያንን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች ለማቃለል የተነደፈውን ብሄራዊ የድርጊት መርሃግብር ስራ ላይ ለማዋል የአፈጻጸም መመሪያዎች እንደሚወጡና የአስፈጻሚ አካላት እንደሚቋቋሙ የሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡</description>
            <link>http://www.waltainfo.com/AmNews/2006/Oct/03Oct06/18807.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">FD1D51B9-534C-11DB-9535-000393197FB0-646-0000003B2F826F4F-FFA</guid>
            <pubDate>Tue, 03 Oct 2006 22:07:21 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>የኦሞ ብሄራዊ ፓርክን ለማደራጀት ከ1 ሚሊየን ዶላር በላይ ወጪ ተመደበ</title>
            <description>የኦሞ ብሄራዊ ፓርክን ለማደራጀት ከ1 ሚሊየን ዶላር በላይ ወጪ ተመደበ&lt;br&gt;&lt;br&gt;
አርባ ምንጭ መስከረም 23/1999/ዋኢማ/ በደቡብ ኦሞ ዞን የሚገኘውን የኦሞ ብሄራዊ ፓርክ በአዲስ መልክ ለማደራጀትና ራሱን ችሎ እንዲንቀሳቀስ ለማድረግ አፍሪካን ፓርክስ የተባለው ተቋም ከአንድ ሚሊየን ዶላር በሚበልጥ ወጪ የማደራጀት ስራዎችን እያካሄደ መሆኑን ገለፀ።</description>
            <link>http://www.waltainfo.com/AmNews/2006/Oct/03Oct06/18806.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">EAA5D6EB-534C-11DB-9535-000393197FB0-646-0000003AF22BBD07-FFA</guid>
            <pubDate>Tue, 03 Oct 2006 22:06:46 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>በክልሉ 24 ሺ 591 ሕፃናት የአራጭ መሰረታዊ ትምህርት ተጠቃሚ እንደሚሆኑ ተገለጸ</title>
            <description>በክልሉ 24 ሺ 591 ሕፃናት የአራጭ መሰረታዊ ትምህርት ተጠቃሚ እንደሚሆኑ ተገለጸ&lt;br&gt;&lt;br&gt;
አሶሳ መስከረም 22/1999/ዋኢማ/ በቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል በተያዘው የትምህርት ዘመን ከ24 ሺ 500 በላይ ሕፃናት የአማራጭ መሰረታዊ ትምህርት ተጠቃሚ እንደሚሆኑ የክልሉ ትምህርት ቢሮ አስታወቀ።</description>
            <link>http://www.waltainfo.com/AmNews/2006/Oct/03Oct06/18803.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">D9EB3DBE-534C-11DB-9535-000393197FB0-646-0000003ABA9AC13C-FFA</guid>
            <pubDate>Tue, 03 Oct 2006 22:06:15 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>በክልሉ ዘጠኝ ሺ ለሚጠጉ የመንግስት ሰራተኞች የአቅም ግንባታ ሥልጠና ተሰጠ</title>
            <description>በክልሉ ዘጠኝ ሺ ለሚጠጉ የመንግስት ሰራተኞች የአቅም ግንባታ ሥልጠና ተሰጠ&lt;br&gt;&lt;br&gt;
ባሕር ዳር መስከረም 23/1999/ዋኢማ/ በአማራ ክልል በወረዳዎች የሚታየውን የማስፈጸም ዓቅም ችግር ለማስወገድ በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት ዘጠኝ ሺ ለሚጠጉ የመንግስት ሰራተኞች ሥልጠና መሰጠቱን የክልሉ ዓቅም ግንባታ ቢሮ ገለፀ።</description>
            <link>http://www.waltainfo.com/AmNews/2006/Oct/03Oct06/18802.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">C7D45473-534C-11DB-9535-000393197FB0-646-0000003A7E84D1B0-FFA</guid>
            <pubDate>Tue, 03 Oct 2006 22:05:47 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>በሱማሌ ክልል የሚገኙ ተማሪዎች መንግስት ለነደፋቸው የልማት ፖሊሲዎች ተግባራዊነት የድርሻቸውን ለመዋጣት ዝግጁነታቸውን ገለጹ</title>
            <description>በሱማሌ ክልል የሚገኙ ተማሪዎች መንግስት ለነደፋቸው የልማት ፖሊሲዎች ተግባራዊነት የድርሻቸውን ለመዋጣት ዝግጁነታቸውን ገለጹ&lt;br&gt;
አምቦ, መስከረም 22 ቀን 1999 (ጅጀጋ) - በሱማሌ ክልል የሚገኙ ተማሪዎች መንግስት ለነደፋቸው የልማት ስትራቴጂዎችና ፖሊሲዎች ተግባራዊነት የድርሻቸውን ለመዋጣት ዝግጁ መሆናቸውን አስታወቁ፡፡&lt;br&gt;
ተማሪዎቹ ላለፉት ዘጠኝ ቀናት በጅጅጋ ከተማ በአብዮታዊ ዲሞክራሲ፣በመልካም አሰተዳደር፣የወጣቱ ሚና በዲሞክራሲና ዲሞክራሲያዊ አንድነትና በገጠር ልማት ስትራቴጂዎችና ፖሊሲዎች ዙሪያ ያደረጉትን ውይይት ዛሬ ሲያጠናቅቁ ባወጡት የአቋም መግለጫ እንደገለጹት መንግስት መልካም አስተዳደርን በማስፈን ሕዝቡ በየደረጃው ተጠቃሚ የሚሆንበትን ፈጣን ልማት ለማምጣት ለነደፋቸው የልማት ስትራቴጂዎችና ፖሊሲዎች ተፈጻሚነት የሚጠበቅባቸውን ሁሉ ያደርጋሉ፡፡</description>
            <link>http://www.ena.gov.et/AmharicNews/2006/Oct/03Oct06/4042.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">8082736A-52E3-11DB-853A-000393197FB0-2035-000004A252399C36-FFA</guid>
            <pubDate>Tue, 03 Oct 2006 09:32:11 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>የድሬዳዋ ነዋሪዎች ስለ ኤች አይ ቪ ኤድስ መረጃ አግኝተው በሽታውን መከላከል እንዲችሉ የሚረዳ ማዕከል በ350 ሺህ ብር ተቋቋመ</title>
            <description>የድሬዳዋ ነዋሪዎች ስለ ኤች አይ ቪ ኤድስ መረጃ አግኝተው በሽታውን መከላከል እንዲችሉ የሚረዳ ማዕከል በ350 ሺህ ብር ተቋቋመ&lt;br&gt;
ድሬዳዋ, መስከረም 22 ቀን 1999 (ድሬዳዋ) - የድሬዳዋ ነዋሪዎች ስለ ኤች አይ ቪ ኤድስ መረጃ አግኝተው በሽታውን መከላከል እንዲችሉ የሚረዳ ማዕከል በ350 ሺህ ብር ተቋቁሞ አገልግሎት መስጠት ጀመረ፡፡&lt;br&gt;
ማዕከሉ ቤተመፃሕፍት፣ በብሮድ ባንድ የታገዘ ነፃ የኢንተርኔት አገልግሎት መስጫ፣ የቪዲዮና ሌሎችም አገልግሎቶች የሚሰጡ ክፍሎች አሉት፡፡</description>
            <link>http://www.ena.gov.et/AmharicNews/2006/Oct/03Oct06/3969.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">6D7F0124-52E3-11DB-853A-000393197FB0-2035-000004A213120187-FFA</guid>
            <pubDate>Tue, 03 Oct 2006 09:31:40 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>በኢትዮጵያ የተጠናከረ የክትባት መርሀ ግብር ማካሄድ የሚያስችል ስልጠና ተጀመረ</title>
            <description>በኢትዮጵያ የተጠናከረ የክትባት መርሀ ግብር ማካሄድ የሚያስችል ስልጠና ተጀመረ&lt;br&gt;
አዳማ, መስከረም 22 ቀን 1999 (አዳማ) - በኢትዮጵያ የተጠናከረ የክትባት መርሀ ግብር ማካሄድ እንዲቻል ዩኒቨርሲቲዎችና የነርስ ማሰልጠኛ ተቋማት ባለሙያዎች ስልጠና በአዳማ ከተማ ዛሬ ተጀመረ፡፡</description>
            <link>http://www.ena.gov.et/AmharicNews/2006/Oct/03Oct06/3995.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">58A42822-52E3-11DB-853A-000393197FB0-2035-000004A1CDCC9B51-FFA</guid>
            <pubDate>Tue, 03 Oct 2006 09:31:08 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>ከውጭ ሲሚንቶ እንዲያስገቡ የሚፈቅድላቸው ባለሃብቶች ሊያሟላቸው የሚገቡ መመዘኛዎች የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ይፋ አደረገ ፡፡</title>
            <description>ከውጭ ሲሚንቶ እንዲያስገቡ የሚፈቅድላቸው ባለሃብቶች ሊያሟላቸው የሚገቡ መመዘኛዎች የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ይፋ አደረገ ፡፡&lt;br&gt;
አዲስ አበባ, መስከረም 22 ቀን 1999 (አዲስ አበባ) -&lt;br&gt;
በአገሪቱ የተፈጠረውን የሲሚንቶ እጥረት ለማቃለል እንዲቻል ከውጭ ሲሚንቶ እንዲያስገቡ የሚፈቅድላቸው ባለሃብቶች ሊያሟላቸው የሚገቡ መመዘኛዎች የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ይፋ አደረገ ፡፡&lt;br&gt;&lt;br&gt;
የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ታደሰ ኀይሌ ዛሬ ለጋዜጠኞች በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ በአሁኑ ወቅት በአገሪቱ የተፈጠረውን የሲሚንቶ እጥረት ለማቃለል መንግስት ለተወሰነ ጊዜ ሲሚንቶ ከንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ጋር በሚደረግ ስምምነት በባለሃብቶች አማካይነት ከውጭ እንዲገባ ፈቅዷል፡፡</description>
            <link>http://www.ena.gov.et/AmharicNews/2006/Oct/03Oct06/4027.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">42CDF370-52E3-11DB-853A-000393197FB0-2035-000004A185444C7C-FFA</guid>
            <pubDate>Tue, 03 Oct 2006 09:30:33 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>የሞስኮ የባህልና የሥነ ጥበብ ዩኒቨርሲቲ በኢትዮጵያ ቅርንጫፍ ለመክፈት ፍላጎት እንዳለው ገለጸ</title>
            <description>የሞስኮ የባህልና የሥነ ጥበብ ዩኒቨርሲቲ በኢትዮጵያ ቅርንጫፍ ለመክፈት ፍላጎት እንዳለው ገለጸ&lt;br&gt;
አዲስ አበባ, መስከረም 22 ቀን 1999 (አዲስ አበባ) - የሞስኮ የባህልና የሥነ ጥበብ ዩኒቨርሲቲ ኢትዮጵያ ውስጥ የባህል ማዕከልና የዩኒቨርሲቲውን ቅርንጫፍ ለመክፈት ፍላጎት እንዳለው መግለጹን በሞስኮ የኢትዮጵያ ኤምባሲ አስታወቀ፡፡</description>
            <link>http://www.ena.gov.et/AmharicNews/2006/Oct/03Oct06/4038.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">CF0D8539-52E2-11DB-853A-000393197FB0-2035-000004A004C9DE99-FFA</guid>
            <pubDate>Tue, 03 Oct 2006 09:27:33 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>የአዲስ አበባ አንዳንድ ነዋሪዎች ለኢሕአዴግ ውሣኔዎች ተግባራዊነት እንደሚንቀሳቀሱ አስታወቁ</title>
            <description>የአዲስ አበባ አንዳንድ ነዋሪዎች ለኢሕአዴግ ውሣኔዎች ተግባራዊነት እንደሚንቀሳቀሱ አስታወቁ&lt;br&gt;&lt;br&gt;&lt;a href=&quot;http://www.ena.gov.et/AmharicNews/2006/Oct/03Oct06/4015.htm&quot;&gt;&lt;img src=&quot;http://www.ena.gov.et/AmharicNews/2006/Oct/03Oct06/Images/4015.jpg&quot; align=&quot;left&quot;&gt;&lt;/a&gt;
አዲስ አበባ, መስከረም 22 ቀን 1999 (አዲስ አበባ) - የኢትዮጵያ ሕዝቦች አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ግንባር /ኢሕአዴግ/ በ6ኛ መደበኛ ጉባዔው ያሳለፋቸው ውሣኔዎች ለአገሪቱ እድገት ከፍተኛ ጠቀሜታ ስለሚኖረው ለተግባራዊነቱ እንደሚንቀሳቀሱ የአዲስ አበባ አንዳንድ ነዋሪዎች አስታወቁ፡፡</description>
            <link>http://www.ena.gov.et/AmharicNews/2006/Oct/03Oct06/4015.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">9CDCA566-52E2-11DB-853A-000393197FB0-2035-0000049F5E13518E-FFA</guid>
            <pubDate>Tue, 03 Oct 2006 09:26:40 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>ኢትዮጵያ በርካታ ጥንታዊ፣ታሪካዊና ባህላዊ የመስህብ ስፍራዎች ቢኖሯትም ከዘርፉ የምታገኘው ገቢ አነስተኛ እንደሆነ ተገለጸ</title>
            <description>ኢትዮጵያ በርካታ ጥንታዊ፣ታሪካዊና ባህላዊ የመስህብ ስፍራዎች ቢኖሯትም ከዘርፉ የምታገኘው ገቢ አነስተኛ እንደሆነ ተገለጸ&lt;br&gt;
አዋሳ, መስከረም 22 ቀን 1999 (አዋሳ) - ኢትዮጵያ በርካታ ጥንታዊ፣ ታሪካዊና ባህላዊ የመስህብ ስፍራዎች ቢኖሯትም ከዘርፉ የምታገኘው ገቢ አነስተኛ መሆኑን የባህልና ቱሪዝም ሚኒስትር ዴኤታ አስታወቁ፡፡&lt;br&gt;
ሚኒስትር ዴኤታዋ ወይዘሮ ታደለች ዳለቾ የዓለም ቱሪዝም ቀንን ምክንያት በማድረግ በአዋሳ ከተማ ዛሬ በተዘጋጀው በፓናል ውይይት ሲከበር እንደተናገሩት አገሪቱ በዓለም አቀፍ የሳይንስ የትምህርትና ባህል ድርጅት/ ዩኔስኮ/ በቅርስነት የተመዘገቡትን ጨምሮ የበርካታ መስህብ ስፍራዎች ባለቤት ብትሆንም ከዘርፉ የምታገኘው ገቢ ከሌሎች የአፍሪካ አገሮች ጋር ሲነፃፀር በጣም አነስተኛ ነው፡፡</description>
            <link>http://www.ena.gov.et/AmharicNews/2006/Oct/03Oct06/4003.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">8F97F387-52E2-11DB-853A-000393197FB0-2035-0000049F3200EE6C-FFA</guid>
            <pubDate>Tue, 03 Oct 2006 09:25:18 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>በአፍሪካ ዘር ማጥፋት የመልካም አስተዳዳር እጦትና ኢዲሞክራሲያዊ አሰራር እንዳይኖር ቁርጠኛ የፖለቲካ ውሳኔ መኖሩ ተገለጸ</title>
            <description>በአፍሪካ ዘር ማጥፋት የመልካም አስተዳዳር እጦትና ኢዲሞክራሲያዊ አሰራር እንዳይኖር ቁርጠኛ የፖለቲካ ውሳኔ መኖሩ ተገለጸ&lt;br&gt;
አዲስ አበባ, መስከረም 22 ቀን 1999 (አዲስ አበባ) - በአፍሪካ ዘር ማጥፋት፣ ግጭት ፣የመልካም አስተዳዳር እጦትና ኢ ዲሞክራሲያዊ አሰራር እንዳይቀጥል ቁርጠኛ የፖለቲካ አቋን መኖሩን የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን አስታወቀ፡፡&lt;br&gt;
የአውሮፓና የአፍሪካ ህብረት የስራ አስፈጻሚ ኮሚሽኖች ስብሰባ ዛሬ አዲስ አበባ ውስጥ ሲጀመር የኮሚሽኑ ሊቀመንበር አልፋ ኦማር ኮናሬ እንደገለጹት ሁለቱ ኮሚሽኖች በአፍሪካ በሰላም ፣ በልማት ፣በማህበራዊ ፣በኢኮኖሚ፣ፖለቲካዊና በሌሎችም መስኮች ተባብሮ መስራት ይጠበቅባቸዋል፡፡</description>
            <link>http://www.ena.gov.et/AmharicNews/2006/Oct/03Oct06/3990.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">7FDDBFD3-52E2-11DB-853A-000393197FB0-2035-0000049EFDC396A3-FFA</guid>
            <pubDate>Tue, 03 Oct 2006 09:24:54 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>አካባቢን ከብክለት ለመጠበቅ አዳዲስ ግኝቶችን መለማመድና ማሳደግ ይገባል.. ፕሬዝዳንት ግርማ</title>
            <description>አካባቢን ከብክለት ለመጠበቅ አዳዲስ ግኝቶችን መለማመድና ማሳደግ ይገባል.. ፕሬዝዳንት ግርማ&lt;br&gt;
አዲስ አበባ, መስከረም 22 ቀን 1999 (አዲስ አበባ) - አካባቢን ከብክለት ለመጠበቅ አዳዲስ ግኝቶችን መለማመድና ማሳደግ እንደሚገባ ፕሬዝዳንት ግርማ ወልደጊዮርጊስ ገለጹ፡፡&lt;br&gt;
የአካባቢ ጥበቃን በተመለከተ ዛሬ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሳይንስ ፋካልቲ በተዘጋጀውና አረንጓዴ መድረክ በሚል በተሰየመው አውደጥናት ላይ ፕሬዝዳንቱ እንዳሉት ስለ ችግር ብቻ ማውራት ተስፋ ቢስ ያደርጋል፡፡ በመሆኑም አዳዲስ ግኝቶችን መቃኘት ይገባል፡፡</description>
            <link>http://www.ena.gov.et/AmharicNews/2006/Oct/03Oct06/3972.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">6F56C51D-52E2-11DB-853A-0003931