Not logged in | Login

ECTV AMHARIC NEWS SEARCH ENGINE

The Latest Ethiopian Amharic News

USE Search for recent news

Unread items (100)

Amharic News, Ethiopian News, ECTV Zena

  • Permalink for 'Amharic_News__Ethiopian_News__ECTV_Zena/2008/06/13/%e1%8b%a8%e1%88%9d%e1%8c%8d%e1%89%a5_%e1%8a%a5%e1%88%85%e1%88%8d_%e1%8a%a5%e1%8c%a5%e1%88%a8%e1%89%b1%e1%8a%93_%e1%8b%a8%e1%89%b0%e1%8c%8e%e1%8c%82%e1%8b%8e%e1%89%bd%e1%8a%95_%e1%89%81%e1%8c%a5%e1%88%ad_%e1%8a%a0%e1%8c%8b%e1%8a%90%e1%8b%8d_%e1%8b%a8%e1%88%9a%e1%8b%ab%e1%89%80%e1%88%ad%e1%89%a1_%e1%8b%88%e1%8c%88%e1%8a%96%e1%89%bd_%e1%8a%a2%e1%8a%ae%e1%8a%96%e1%88%9a%e1%8b%ab%e1%8b%8a_%e1%8a%a5%e1%8b%b5%e1%8c%88%e1%89%b1%e1%8a%95_%e1%88%88%e1%88%9b%e1%8c%a3%e1%8c%a3%e1%88%8d_%e1%8b%a8%e1%88%9a%e1%8d%88%e1%88%8d%e1%8c%89_%e1%88%98%e1%88%86%e1%8a%93%e1%89%b8%e1%8b%8d_%e1%89%b0%e1%8c%88%e1%88%88%e1%8d%80'

    የምግብ እህል እጥረቱና የተጎጂዎችን ቁጥር አጋነው የሚያቀርቡ ወገኖች ኢኮኖሚያዊ እድገቱን ለማጣጣል የሚፈልጉ መሆናቸው ተገለፀ

    Posted: June 13th, 2008, 11:34am EDT
    አዲስ አበባ ሰኔ 5/2000/ዋኢማ/ በኢትዮጵያ ያጋጠመውን የምግብ እህል እጥረትና የተጎጂዎችን ቁጥር አጋነው የሚያቀርቡ ወገኖች በአገሪቱ እየተመዘገበ ያለውን ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ለማጣጣል የሚፈልጉና በጉዳዩ የራሳቸውን ጥቅም አብረው የሚያሰሉ መሆናቸውን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የግብርናና ገጠር ልማት ሚኒስትር አስታወቁ።
    ሚኒስትሩ አቶ አዲሱ ለገሰ ዛሬ በጽህፈት ቤታቸው በሰጡት መግለጫ እንዳስታወቁት፤ አንዳንድ በአስቸኳይ እርዳታ ላይ የተመሰረተ ተግባር የሚያከናውኑ ወገኖች የተረጂዎች ቁጥር መቀነስን በህልውናቸው ላይ የመጣ አደጋ አድርገው እንደሚቆጥሩት ጠቅሰው፤ ብዙ እርዳታ እንዲገኝ ቁጥሩን በርከት አድርገን እናቅርብ የሚል ሃሳብ ሲያቀርቡ መቆየታቸውን ገልፀዋል።

    ከበልግ ዝናብ ዕጥረት ጋር በተያያዘ በተወሰኑ በልግ አብቃይ አካባቢዎች የምግብ እህል እጥረት ያጋጠማቸው ዜጎች ቁጥር 4 ነጥብ 6 ሚሊየን መሆኑን አቶ አዲሱ አስታውቀው፣ መንግስት ለተረጂዎች ተገቢውን ድጋፍ እያደረገ መሆኑንና የተረጂዎችን ቁጥር በተመለከተ በአንዳንድ ወገኖች የሚቀርበው አሃዝ እጅግ የተጋነነ እንደሆነ ገልጸዋል።

    የተጎጂዎችን ቁጥር በተመለከተ የተዛቡና ወጥነት የሌላቸው አሀዞች በተለያዩ ወገኖች ሲቀርቡ የቆዩ ቢሆንም መንግስት ችግሩ በተከሰተባቸው አካባቢዎች ባደረገው ጥናት የምግብ እህል እጥረት ያጋጠማቸው ዜጎች ቁጥር 4 ሚሊየን 617 ሺ 300 መሆኑ ተረጋግጧል።

    መንግስት በጉዳዩ ላይ ተገቢው ጥናት ከተካሄደ በኋላ ትክክለኛውን አሃዝ የመግለጽ አማራጭን መከተሉን የገለጹት አቶ አዲሱ፤ ይህን ያደረገውም በዓለም አደባባይ በልመና ተወዳዳሪ መሆን የሚያኮራ ድርጊት አለመሆኑን በመገንዘብ እንደሆነ አቶ አዲሱ አመልክተዋል።

    በሴፍትኔት የታቀፉ ወገኖችን ጭምር እንደሚያካትት የገለጹት አቶ አዲሱ፤ ከዚህ ውስጥ ክትትልና ድጋፍ የሚፈልጉት ከአምስት ዓመት በታች ያሉ ህጻናት ቁጥር 75 ሺ ብቻ መሆኑን ጠቁመዋል።

    መንግስት በእርዳታ ሰጪ ድርጅቶች የቀረቡ በግምት ላይ የተመሰረቱና የተጋነኑ መረጃዎች በጥናት እንዲረጋገጡ ማድረጉንና ከጥናቱ ጎን ለጎንም ለተጎጂ ወገኖች እርዳታ ማቅረቡን ገልጸው፤ የምግብ እህል እጥረቱ በደቡብ ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች፣ በኦሮሚያ፣ በሶማሌ፣ በአማራና ትግራይ ክልሎች በሚገኙ አንዳንድ ወረዳዎች ማጋጠሙን ተናግረዋል።

    ተጎጂዎች ያጋጠማቸውን ችግር ለማቃለል በተደረገ ጥረት ካለፈው የካቲት ጀምሮ ከ775 ሺ ኩንታል የሚበልጥ እህል ለተጎጂዎች መከፋፈሉን ጠቁመው፤ 50 ሚሊየን ብር በጀት በመመደብ የህክምና አገልግሎት መሰጠቱን ገልጸዋል።

    በአካባቢዎቹ ያጋጠመውን የውሃ እጥረት ለማቃለል የነባር ጉድጓዶችን ጥልቀት በመጨመርና በቦቴ በማመላለስ ጥረት መደረጉን ያመለከቱት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ በአርብቶ አደር አካባቢዎች ለእንስሳት መኖ የማቅረብና ለአርቢዎች ገበያ የማፈላለግ ድጋፍ መደረጉን ገልጸዋል ።

    መንግስት ከደጋፊዎቹ ጋር በመሆን እያደረገ ያለውን የምግብ እህልና አልሚ ምግብ የማቅረብ ተግባር አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸው፤ ባለፈው ግንቦት ወር የተገኘውን ዝናብ በመጠቀምም ቶሎ ሊደርሱ የሚችሉ ሰብሎችን በመዝራት የማካካስ ስራ እየተሰራ መሆኑን መናገራቸውን ዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል ዘግቧል።

WALTA INFORMATION CENTER, AMHARIC NEWS

  • Permalink for 'WALTA_INFORMATION_CENTER__AMHARIC_NEWS/2008/06/13/%e1%8b%a8%e1%88%9d%e1%8c%8d%e1%89%a5_%e1%8a%a5%e1%88%85%e1%88%8d_%e1%8a%a5%e1%8c%a5%e1%88%a8%e1%89%b1%e1%8a%93_%e1%8b%a8%e1%89%b0%e1%8c%8e%e1%8c%82%e1%8b%8e%e1%89%bd%e1%8a%95_%e1%89%81%e1%8c%a5%e1%88%ad_%e1%8a%a0%e1%8c%8b%e1%8a%90%e1%8b%8d_%e1%8b%a8%e1%88%9a%e1%8b%ab%e1%89%80%e1%88%ad%e1%89%a1_%e1%8b%88%e1%8c%88%e1%8a%96%e1%89%bd_%e1%8a%a2%e1%8a%ae%e1%8a%96%e1%88%9a%e1%8b%ab%e1%8b%8a_%e1%8a%a5%e1%8b%b5%e1%8c%88%e1%89%b1%e1%8a%95_%e1%88%88%e1%88%9b%e1%8c%a3%e1%8c%a3%e1%88%8d_%e1%8b%a8%e1%88%9a%e1%8d%88%e1%88%8d%e1%8c%89_%e1%88%98%e1%88%86%e1%8a%93%e1%89%b8%e1%8b%8d_%e1%89%b0%e1%8c%88%e1%88%88%e1%8d%80'

    የምግብ እህል እጥረቱና የተጎጂዎችን ቁጥር አጋነው የሚያቀርቡ ወገኖች ኢኮኖሚያዊ እድገቱን ለማጣጣል የሚፈልጉ መሆናቸው ተገለፀ

    Posted: June 13th, 2008, 11:34am EDT
    አዲስ አበባ ሰኔ 5/2000/ዋኢማ/ በኢትዮጵያ ያጋጠመውን የምግብ እህል እጥረትና የተጎጂዎችን ቁጥር አጋነው የሚያቀርቡ ወገኖች በአገሪቱ እየተመዘገበ ያለውን ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ለማጣጣል የሚፈልጉና በጉዳዩ የራሳቸውን ጥቅም አብረው የሚያሰሉ መሆናቸውን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የግብርናና ገጠር ልማት ሚኒስትር አስታወቁ።
    ሚኒስትሩ አቶ አዲሱ ለገሰ ዛሬ በጽህፈት ቤታቸው በሰጡት መግለጫ እንዳስታወቁት፤ አንዳንድ በአስቸኳይ እርዳታ ላይ የተመሰረተ ተግባር የሚያከናውኑ ወገኖች የተረጂዎች ቁጥር መቀነስን በህልውናቸው ላይ የመጣ አደጋ አድርገው እንደሚቆጥሩት ጠቅሰው፤ ብዙ እርዳታ እንዲገኝ ቁጥሩን በርከት አድርገን እናቅርብ የሚል ሃሳብ ሲያቀርቡ መቆየታቸውን ገልፀዋል።

    ከበልግ ዝናብ ዕጥረት ጋር በተያያዘ በተወሰኑ በልግ አብቃይ አካባቢዎች የምግብ እህል እጥረት ያጋጠማቸው ዜጎች ቁጥር 4 ነጥብ 6 ሚሊየን መሆኑን አቶ አዲሱ አስታውቀው፣ መንግስት ለተረጂዎች ተገቢውን ድጋፍ እያደረገ መሆኑንና የተረጂዎችን ቁጥር በተመለከተ በአንዳንድ ወገኖች የሚቀርበው አሃዝ እጅግ የተጋነነ እንደሆነ ገልጸዋል።

    የተጎጂዎችን ቁጥር በተመለከተ የተዛቡና ወጥነት የሌላቸው አሀዞች በተለያዩ ወገኖች ሲቀርቡ የቆዩ ቢሆንም መንግስት ችግሩ በተከሰተባቸው አካባቢዎች ባደረገው ጥናት የምግብ እህል እጥረት ያጋጠማቸው ዜጎች ቁጥር 4 ሚሊየን 617 ሺ 300 መሆኑ ተረጋግጧል።

    መንግስት በጉዳዩ ላይ ተገቢው ጥናት ከተካሄደ በኋላ ትክክለኛውን አሃዝ የመግለጽ አማራጭን መከተሉን የገለጹት አቶ አዲሱ፤ ይህን ያደረገውም በዓለም አደባባይ በልመና ተወዳዳሪ መሆን የሚያኮራ ድርጊት አለመሆኑን በመገንዘብ እንደሆነ አቶ አዲሱ አመልክተዋል።

    በሴፍትኔት የታቀፉ ወገኖችን ጭምር እንደሚያካትት የገለጹት አቶ አዲሱ፤ ከዚህ ውስጥ ክትትልና ድጋፍ የሚፈልጉት ከአምስት ዓመት በታች ያሉ ህጻናት ቁጥር 75 ሺ ብቻ መሆኑን ጠቁመዋል።

    መንግስት በእርዳታ ሰጪ ድርጅቶች የቀረቡ በግምት ላይ የተመሰረቱና የተጋነኑ መረጃዎች በጥናት እንዲረጋገጡ ማድረጉንና ከጥናቱ ጎን ለጎንም ለተጎጂ ወገኖች እርዳታ ማቅረቡን ገልጸው፤ የምግብ እህል እጥረቱ በደቡብ ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች፣ በኦሮሚያ፣ በሶማሌ፣ በአማራና ትግራይ ክልሎች በሚገኙ አንዳንድ ወረዳዎች ማጋጠሙን ተናግረዋል።

    ተጎጂዎች ያጋጠማቸውን ችግር ለማቃለል በተደረገ ጥረት ካለፈው የካቲት ጀምሮ ከ775 ሺ ኩንታል የሚበልጥ እህል ለተጎጂዎች መከፋፈሉን ጠቁመው፤ 50 ሚሊየን ብር በጀት በመመደብ የህክምና አገልግሎት መሰጠቱን ገልጸዋል።

    በአካባቢዎቹ ያጋጠመውን የውሃ እጥረት ለማቃለል የነባር ጉድጓዶችን ጥልቀት በመጨመርና በቦቴ በማመላለስ ጥረት መደረጉን ያመለከቱት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ በአርብቶ አደር አካባቢዎች ለእንስሳት መኖ የማቅረብና ለአርቢዎች ገበያ የማፈላለግ ድጋፍ መደረጉን ገልጸዋል ።

    መንግስት ከደጋፊዎቹ ጋር በመሆን እያደረገ ያለውን የምግብ እህልና አልሚ ምግብ የማቅረብ ተግባር አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸው፤ ባለፈው ግንቦት ወር የተገኘውን ዝናብ በመጠቀምም ቶሎ ሊደርሱ የሚችሉ ሰብሎችን በመዝራት የማካካስ ስራ እየተሰራ መሆኑን መናገራቸውን ዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል ዘግቧል።

Amharic News, Ethiopian News, ECTV Zena

  • Permalink for 'Amharic_News__Ethiopian_News__ECTV_Zena/2008/06/13/%e1%8b%a8%e1%8a%a8%e1%8d%8d%e1%89%b0%e1%8a%9b_%e1%89%b5%e1%88%9d%e1%88%85%e1%88%ad%e1%89%b5_%e1%89%b0%e1%89%8b%e1%88%9b%e1%89%b5_%e1%89%b0%e1%88%9b%e1%88%aa%e1%8b%8e%e1%89%bd_%e1%8a%a8%e1%88%b5%e1%8a%ac%e1%89%b3%e1%88%9b_%e1%88%b0%e1%8b%8e%e1%89%bd_%e1%8b%a8%e1%88%9a%e1%8b%ab%e1%8c%88%e1%8a%99%e1%89%b5_%e1%89%b0%e1%88%98%e1%8a%ad%e1%88%ae_%e1%8c%a0%e1%89%83%e1%88%9a_%e1%88%98%e1%88%86%e1%8a%91_%e1%89%b0%e1%8c%88%e1%88%88%e1%8d%80'

    የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ከስኬታማ ሰዎች የሚያገኙት ተመክሮ ጠቃሚ መሆኑ ተገለፀ

    Posted: June 13th, 2008, 11:32am EDT
    አዲስ አበባ ሰኔ 5/2000 ዋኢማ/የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች በትምህርት ገበታ ከሚያገኙት የቀለም ትምህርት በተጨማሪ በተለያዩ መስኮች ከተሰማሩ ባለሙያዎች የሚያገኙት ተመክሮ ወደ ስራ አለም ሲሸጋገሩ እንደሚያግዛቸው ክቡር ዶክተር አትሌት ሻለቃ ኃይሌ ገብረስላሴ ገለፀ።


    አትሌት ሻለቃ ኃይሌ ትናንት በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ቴክኖሎጂ ፋኩልቲ አዳራሽ ስለሙያው ስኬትና ተያያዥነት ባላቸው ጉዳዮች ላይ ከተማሪዎች ጋር ውይይት ባደረገበት ወቅት አንደገለፀው፤ ተማሪዎች በዩኒቨርስቲው ያገኙትን ትምህርት ተከታትለው ተመርቀው ከወጡ በኋላ በሚገባ መተግበር የሚያስችሉ ተሞክሮዎችን ማግኘት አለባቸው።

    ተማሪዎቹም ሆኑ መምህራኑ የቆሙለትን ዓላማ ለማሳካት ጠንክረው በመስራት ለውጤት መብቃት እንደሚችሉ የገለፀው አትሌት ኃይሌ ፅናትን ተላበሶ የሰራ ሰው ስኬታማ መሆኑ አያጠራጥርም ብሏል።

    አገራችን በአሁኑ ወቅት በሰፊ የልማትና የእድገት እንቅስቃሴ ላይ በመሆኗ የተማሩ ኃይሎች ይህንን ልማት የበለጠ ለማጎልበት ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ መስራት እንደሚጠበቅባቸው አስረድቷል።

    ሩጫ ሲጀምር በተሳተፈበት ውድድር 99ኛ የወጣበት ወቅት እንደነበረና በወቅቱ አባቱን ጨምሮ ሌሎች ወዳጆቹ ሩጫ ጠቀሜታ እንደሌለው ቢገልፁለትም በእልህና ተስፋ ባለመቁረጥ ባደረገው ጥረት ከ25 በላይ ሪከርዶችን ሊያስመዘግብ መቻሉንና ሰው ከጣረ ካቀደው በላይ መሄድ ይችላል ብሏል።

    በቢዝነሱም በኩል ጤናማ የሆነ ልማትና ዕድገት ለማመጣት የሚያስችሉ ስልቶችን በመከተል እየሰራ እንደሆነና አሁን ያለውን ስኬት የበለጠ በመስራት ለማሳደግ ቀን ከሌት እየሰራ መሆኑን አትሌት ሻለቃ ኃይሌ ተናግሯል።

    በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የኢንደስትሪ ፓርትነርሽፕ ፕሮግራም ዳይሬክተር ዶክተር ኢንጀነር ዳንኤል ቅጣው በዚህ ወቅት እንደገለጹት፤ ይህ አይነቱ መድረክ በተለያዩ የሙያ ስምሪቶች የተሳካላቸውን ሰዎች በመጋበዝ የተማሪዎችን ግንዛቤ ማሰፋትና የህይወት መርሆችን እንዲረዱ ማድረግን አላማ ያደረገ ነው ብለዋል።

    በቀጣይም ሰፊ ተሞክሮ ያላቸውንና በለይም በቢዝነስ፣ በኮንስትራክሽንና በተዛማች ዘርፎች ላይ በማተኮር ባለሙያዎችን በመጋበዝ እንደሚያወያዩም ዳይሬክተሩ ገልፀዋል።

    አትሌት ሻለቃ ኃይሌ ገብረስላሴ ለቴክኖሎጂ ፋኩልቲ ተማሪዎች የትምህርት አገልግሎት የሚውል ከ400 የሚበልጥ የራየቲንግ ፓድ በስጦታ ለተማሪዎች አከፋፍሏል።

    በዩኒቨርስቲው የመካኒካል ኢንጅነሪንግ የመጀመሪያ ዲግሪ፤ የድህረ ምረቃ፤ የፒኤችዲ እጩ ተመራቂዎችና መምህራንን ጨምሮ ከ500 በላይ ተሳታፊዎች ኃይሌ በስፖርቱና በቢዝነስ ላይ ያገኘውን ስኬት አስመልክተው የግማሽ ቀን ውይይት ማድረጋቸውን ዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል ዘገቧል።

WALTA INFORMATION CENTER, AMHARIC NEWS

  • Permalink for 'WALTA_INFORMATION_CENTER__AMHARIC_NEWS/2008/06/13/%e1%8b%a8%e1%8a%a8%e1%8d%8d%e1%89%b0%e1%8a%9b_%e1%89%b5%e1%88%9d%e1%88%85%e1%88%ad%e1%89%b5_%e1%89%b0%e1%89%8b%e1%88%9b%e1%89%b5_%e1%89%b0%e1%88%9b%e1%88%aa%e1%8b%8e%e1%89%bd_%e1%8a%a8%e1%88%b5%e1%8a%ac%e1%89%b3%e1%88%9b_%e1%88%b0%e1%8b%8e%e1%89%bd_%e1%8b%a8%e1%88%9a%e1%8b%ab%e1%8c%88%e1%8a%99%e1%89%b5_%e1%89%b0%e1%88%98%e1%8a%ad%e1%88%ae_%e1%8c%a0%e1%89%83%e1%88%9a_%e1%88%98%e1%88%86%e1%8a%91_%e1%89%b0%e1%8c%88%e1%88%88%e1%8d%80'

    የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ከስኬታማ ሰዎች የሚያገኙት ተመክሮ ጠቃሚ መሆኑ ተገለፀ

    Posted: June 13th, 2008, 11:32am EDT
    አዲስ አበባ ሰኔ 5/2000 ዋኢማ/የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች በትምህርት ገበታ ከሚያገኙት የቀለም ትምህርት በተጨማሪ በተለያዩ መስኮች ከተሰማሩ ባለሙያዎች የሚያገኙት ተመክሮ ወደ ስራ አለም ሲሸጋገሩ እንደሚያግዛቸው ክቡር ዶክተር አትሌት ሻለቃ ኃይሌ ገብረስላሴ ገለፀ።


    አትሌት ሻለቃ ኃይሌ ትናንት በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ቴክኖሎጂ ፋኩልቲ አዳራሽ ስለሙያው ስኬትና ተያያዥነት ባላቸው ጉዳዮች ላይ ከተማሪዎች ጋር ውይይት ባደረገበት ወቅት አንደገለፀው፤ ተማሪዎች በዩኒቨርስቲው ያገኙትን ትምህርት ተከታትለው ተመርቀው ከወጡ በኋላ በሚገባ መተግበር የሚያስችሉ ተሞክሮዎችን ማግኘት አለባቸው።

    ተማሪዎቹም ሆኑ መምህራኑ የቆሙለትን ዓላማ ለማሳካት ጠንክረው በመስራት ለውጤት መብቃት እንደሚችሉ የገለፀው አትሌት ኃይሌ ፅናትን ተላበሶ የሰራ ሰው ስኬታማ መሆኑ አያጠራጥርም ብሏል።

    አገራችን በአሁኑ ወቅት በሰፊ የልማትና የእድገት እንቅስቃሴ ላይ በመሆኗ የተማሩ ኃይሎች ይህንን ልማት የበለጠ ለማጎልበት ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ መስራት እንደሚጠበቅባቸው አስረድቷል።

    ሩጫ ሲጀምር በተሳተፈበት ውድድር 99ኛ የወጣበት ወቅት እንደነበረና በወቅቱ አባቱን ጨምሮ ሌሎች ወዳጆቹ ሩጫ ጠቀሜታ እንደሌለው ቢገልፁለትም በእልህና ተስፋ ባለመቁረጥ ባደረገው ጥረት ከ25 በላይ ሪከርዶችን ሊያስመዘግብ መቻሉንና ሰው ከጣረ ካቀደው በላይ መሄድ ይችላል ብሏል።

    በቢዝነሱም በኩል ጤናማ የሆነ ልማትና ዕድገት ለማመጣት የሚያስችሉ ስልቶችን በመከተል እየሰራ እንደሆነና አሁን ያለውን ስኬት የበለጠ በመስራት ለማሳደግ ቀን ከሌት እየሰራ መሆኑን አትሌት ሻለቃ ኃይሌ ተናግሯል።

    በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የኢንደስትሪ ፓርትነርሽፕ ፕሮግራም ዳይሬክተር ዶክተር ኢንጀነር ዳንኤል ቅጣው በዚህ ወቅት እንደገለጹት፤ ይህ አይነቱ መድረክ በተለያዩ የሙያ ስምሪቶች የተሳካላቸውን ሰዎች በመጋበዝ የተማሪዎችን ግንዛቤ ማሰፋትና የህይወት መርሆችን እንዲረዱ ማድረግን አላማ ያደረገ ነው ብለዋል።

    በቀጣይም ሰፊ ተሞክሮ ያላቸውንና በለይም በቢዝነስ፣ በኮንስትራክሽንና በተዛማች ዘርፎች ላይ በማተኮር ባለሙያዎችን በመጋበዝ እንደሚያወያዩም ዳይሬክተሩ ገልፀዋል።

    አትሌት ሻለቃ ኃይሌ ገብረስላሴ ለቴክኖሎጂ ፋኩልቲ ተማሪዎች የትምህርት አገልግሎት የሚውል ከ400 የሚበልጥ የራየቲንግ ፓድ በስጦታ ለተማሪዎች አከፋፍሏል።

    በዩኒቨርስቲው የመካኒካል ኢንጅነሪንግ የመጀመሪያ ዲግሪ፤ የድህረ ምረቃ፤ የፒኤችዲ እጩ ተመራቂዎችና መምህራንን ጨምሮ ከ500 በላይ ተሳታፊዎች ኃይሌ በስፖርቱና በቢዝነስ ላይ ያገኘውን ስኬት አስመልክተው የግማሽ ቀን ውይይት ማድረጋቸውን ዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል ዘገቧል።

Amharic News, Ethiopian News, ECTV Zena

  • Permalink for 'Amharic_News__Ethiopian_News__ECTV_Zena/2008/05/19/%e1%8b%a8%e1%8a%a4%e1%88%ad%e1%89%b5%e1%88%ab_%e1%88%98%e1%8c%88%e1%8a%93%e1%8a%9b_%e1%89%a5%e1%8b%99%e1%8a%8b%e1%8a%95_%e1%8b%a8%e1%8c%8e%e1%88%a8%e1%89%a4%e1%89%b5_%e1%8a%a0%e1%8c%88%e1%88%ae%e1%89%bd_%e1%88%b0%e1%88%8b%e1%88%9d%e1%8a%95_%e1%89%a0%e1%88%9b%e1%8b%b0%e1%8d%8d%e1%88%a8%e1%88%b5_%e1%89%b0%e1%8c%8d%e1%89%a3%e1%88%ad_%e1%88%8b%e1%8b%ad_%e1%88%98%e1%8c%a0%e1%88%98%e1%8b%b3%e1%89%b8%e1%8b%8d_%e1%89%b0%e1%8c%88%e1%88%88%e1%8c%b8'

    የኤርትራ መገናኛ ብዙኋን የጎረቤት አገሮች ሰላምን በማደፍረስ ተግባር ላይ መጠመዳቸው ተገለጸ

    Posted: May 19th, 2008, 7:36am EDT
    መቀሌ ግንቦት 10/2000/ዋኢማ/ የኤርትራ መገናኛ ብዙኋን የአገሪቱን አንገብጋቢ የሰላም፤የዴሞክራሲና የልማት ጉዳዮች ላይ ከማትኮር ይልቅ በጎረቤት አገሮች ሰላም ማደፍረስ ተግባር ላይ መጠመዳቸው አሳፋሪ ተግባር መሆኑን ሰሞኑን ወደ ኢትዮጵያ የገባ ኤርትራዊ ጋዜጠኛ አስታወቀ ።

    የኤርትራ መንግሥት የግፍ አገዛዝን በመቃወም ሰሞኑን ወደ ኢትዮጵያ የገባው በኤርትራ ቴሌቪዥንና ሬድዮ ይሰራ የነበረው ጋዜጠኛ ገብረመድህን አብረሃ እንደገለጸው፤የኤርትራ ህዝብ በሻዕቢያ የሚደርስበት ስቃይና መከራ በአሁኑ ወቅት አስከፊ ደረጃ ላይ ደርሷል ።

    የሻዕቢያ መንግስት የሚቆጣጠራቸው የኤርትራ መገናኛ ብዙኋን የአገሪቱን አንገብጋቢ ጥያቄዎች የሆኑ የሰላም፤የዴሞክራሲና የልማት ጉዳዮች ላይ ከማትኮር ይልቅ ዋነኛ አጀንዳቸውና ጊዚያቸው በጎሮቤት አገሮች አልቧልታ ላይ መጠመዳቸውን አመልክቷል ።

    የኤርትራ ህዝብ ህልውና ከባድ ፈተና ውስጥ በወደቀበት በአሁኑ ወቅት የኢሳያስ መንግስት የኤርትራ ሃብትና ንብረትን የጎሮቤት አገሮች የውስጥ ጉዳይን ለማተራመስና ተቃዋሚ ድርጅቶች ለመደገፍ እያዋለው እንደሚገኝ ገልጾ የኤርትራ ህዝብ ስለራሱ የውስጥ ጉዳይ የሚመክርበት የሰላም አየር ለማምጣት ሻዕቢያን በቃህ ሊለው ይገባል ብሏል።

    ኤርትራ ዜጎቿ የመናገርና የማሰብ መብታቸው አጥተው የሲኦል ኑሮ እንዲገፉ ተገደዋል ያለው ጋዜጠኛ ገብረመድህን በስርዓቱ የተማረሩ ወጣቶች ህይወታቸውን ለማቆየት ወደ ተለያዩ አገሮች መሰደድ ብቸኛው አማራጭ እየሆነ መምጣቱን ገልጿል።

    ብዙሃን ኤርትራውያን ከፖለቲካዊ ስልጣንና ከልማቱ ተገልለው የኢሳያስን አገዛዝ አሜን ብለው እንዲቀበሉ በመሳሪያ ሃይል በታፈኑበት በአሁኑ ወቅት ጥቂት ባለሥልጣናትና ወታደራዊ አዛዦች እንዳሻቸው የሚፈነጩባት አገር እንደሆነች መታዘቡን ገልጿል።

    አገሪቱን ለመምራት ህጋዊ መሰረትም ሆነ ተጠያቂነት የሌለው የኢሳያስ መንግሥት ኤርትራን እንደአገር ለጥፋት እየዳረጋት በሚገኝበትና የተለየ አመለካከት የያዙ ዜጎቿ በሚታሰሩባትና በሚገደሉባት በአሁኑ ወቅት የኤርትራ መገናኛ ብዙኋን ኤርትራ ወንጀል የማይፈጸምባት ብቸኛ አገር ነች የሚል መዝሙር መስማት የተለመደ ቅጥፈት መሆኑን አብራርቷል።

    የኤርትራ ህዝብ ካሁን ወዲያ የሻዕቢያን የግፍ አገዛዝ ተሸክሞ የሚያዘግምበት ወቅት እያከተመ መሆኑን የተናገረው ጋዜጠኛ ገብረመድህን ሁሉም ዜጋ ለኤርትራ ህዝብና ለአካባቢው ሰላም ጠንቅ የሆነውን ስርዓት ለመጣል መነሳሳት እንዳለበት ጥሪ ማቅረቡን ዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል ዘግቧል።

WALTA INFORMATION CENTER, AMHARIC NEWS

  • Permalink for 'WALTA_INFORMATION_CENTER__AMHARIC_NEWS/2008/05/19/%e1%8b%a8%e1%8a%a4%e1%88%ad%e1%89%b5%e1%88%ab_%e1%88%98%e1%8c%88%e1%8a%93%e1%8a%9b_%e1%89%a5%e1%8b%99%e1%8a%8b%e1%8a%95_%e1%8b%a8%e1%8c%8e%e1%88%a8%e1%89%a4%e1%89%b5_%e1%8a%a0%e1%8c%88%e1%88%ae%e1%89%bd_%e1%88%b0%e1%88%8b%e1%88%9d%e1%8a%95_%e1%89%a0%e1%88%9b%e1%8b%b0%e1%8d%8d%e1%88%a8%e1%88%b5_%e1%89%b0%e1%8c%8d%e1%89%a3%e1%88%ad_%e1%88%8b%e1%8b%ad_%e1%88%98%e1%8c%a0%e1%88%98%e1%8b%b3%e1%89%b8%e1%8b%8d_%e1%89%b0%e1%8c%88%e1%88%88%e1%8c%b8'

    የኤርትራ መገናኛ ብዙኋን የጎረቤት አገሮች ሰላምን በማደፍረስ ተግባር ላይ መጠመዳቸው ተገለጸ

    Posted: May 19th, 2008, 7:36am EDT
    መቀሌ ግንቦት 10/2000/ዋኢማ/ የኤርትራ መገናኛ ብዙኋን የአገሪቱን አንገብጋቢ የሰላም፤የዴሞክራሲና የልማት ጉዳዮች ላይ ከማትኮር ይልቅ በጎረቤት አገሮች ሰላም ማደፍረስ ተግባር ላይ መጠመዳቸው አሳፋሪ ተግባር መሆኑን ሰሞኑን ወደ ኢትዮጵያ የገባ ኤርትራዊ ጋዜጠኛ አስታወቀ ።

    የኤርትራ መንግሥት የግፍ አገዛዝን በመቃወም ሰሞኑን ወደ ኢትዮጵያ የገባው በኤርትራ ቴሌቪዥንና ሬድዮ ይሰራ የነበረው ጋዜጠኛ ገብረመድህን አብረሃ እንደገለጸው፤የኤርትራ ህዝብ በሻዕቢያ የሚደርስበት ስቃይና መከራ በአሁኑ ወቅት አስከፊ ደረጃ ላይ ደርሷል ።

    የሻዕቢያ መንግስት የሚቆጣጠራቸው የኤርትራ መገናኛ ብዙኋን የአገሪቱን አንገብጋቢ ጥያቄዎች የሆኑ የሰላም፤የዴሞክራሲና የልማት ጉዳዮች ላይ ከማትኮር ይልቅ ዋነኛ አጀንዳቸውና ጊዚያቸው በጎሮቤት አገሮች አልቧልታ ላይ መጠመዳቸውን አመልክቷል ።

    የኤርትራ ህዝብ ህልውና ከባድ ፈተና ውስጥ በወደቀበት በአሁኑ ወቅት የኢሳያስ መንግስት የኤርትራ ሃብትና ንብረትን የጎሮቤት አገሮች የውስጥ ጉዳይን ለማተራመስና ተቃዋሚ ድርጅቶች ለመደገፍ እያዋለው እንደሚገኝ ገልጾ የኤርትራ ህዝብ ስለራሱ የውስጥ ጉዳይ የሚመክርበት የሰላም አየር ለማምጣት ሻዕቢያን በቃህ ሊለው ይገባል ብሏል።

    ኤርትራ ዜጎቿ የመናገርና የማሰብ መብታቸው አጥተው የሲኦል ኑሮ እንዲገፉ ተገደዋል ያለው ጋዜጠኛ ገብረመድህን በስርዓቱ የተማረሩ ወጣቶች ህይወታቸውን ለማቆየት ወደ ተለያዩ አገሮች መሰደድ ብቸኛው አማራጭ እየሆነ መምጣቱን ገልጿል።

    ብዙሃን ኤርትራውያን ከፖለቲካዊ ስልጣንና ከልማቱ ተገልለው የኢሳያስን አገዛዝ አሜን ብለው እንዲቀበሉ በመሳሪያ ሃይል በታፈኑበት በአሁኑ ወቅት ጥቂት ባለሥልጣናትና ወታደራዊ አዛዦች እንዳሻቸው የሚፈነጩባት አገር እንደሆነች መታዘቡን ገልጿል።

    አገሪቱን ለመምራት ህጋዊ መሰረትም ሆነ ተጠያቂነት የሌለው የኢሳያስ መንግሥት ኤርትራን እንደአገር ለጥፋት እየዳረጋት በሚገኝበትና የተለየ አመለካከት የያዙ ዜጎቿ በሚታሰሩባትና በሚገደሉባት በአሁኑ ወቅት የኤርትራ መገናኛ ብዙኋን ኤርትራ ወንጀል የማይፈጸምባት ብቸኛ አገር ነች የሚል መዝሙር መስማት የተለመደ ቅጥፈት መሆኑን አብራርቷል።

    የኤርትራ ህዝብ ካሁን ወዲያ የሻዕቢያን የግፍ አገዛዝ ተሸክሞ የሚያዘግምበት ወቅት እያከተመ መሆኑን የተናገረው ጋዜጠኛ ገብረመድህን ሁሉም ዜጋ ለኤርትራ ህዝብና ለአካባቢው ሰላም ጠንቅ የሆነውን ስርዓት ለመጣል መነሳሳት እንዳለበት ጥሪ ማቅረቡን ዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል ዘግቧል።

Amharic News, Ethiopian News, ECTV Zena

  • Permalink for 'Amharic_News__Ethiopian_News__ECTV_Zena/2008/05/17/%e1%8b%a8%e1%8a%a2%e1%89%b5%e1%8b%ae_%e1%88%b1%e1%8b%b3%e1%8a%95%e1%8a%95_%e1%8b%b5%e1%8a%95%e1%89%a0%e1%88%ad_%e1%89%a0%e1%89%b0%e1%88%98%e1%88%88%e1%8a%a8%e1%89%b0_%e1%88%9a%e1%8b%b2%e1%8b%ab%e1%8b%8e%e1%89%bd_%e1%8b%ab%e1%88%b5%e1%89%b0%e1%88%8b%e1%88%88%e1%8d%89%e1%89%b5_%e1%8b%98%e1%8c%88%e1%89%a3_%e1%8a%a8%e1%8b%95%e1%8b%8d%e1%8a%90%e1%89%b5_%e1%8b%a8%e1%88%ab%e1%89%80_%e1%88%98%e1%88%86%e1%8a%91_%e1%89%b0%e1%8c%88%e1%88%88%e1%8d%80'

    የኢትዮ ሱዳንን ድንበር በተመለከተ ሚዲያዎች ያስተላለፉት ዘገባ ከዕውነት የራቀ መሆኑ ተገለፀ

    Posted: May 17th, 2008, 9:07am EDT
    አዲስ አበባ ግንቦት 7/2000/ዋኢማ/የኢትዮ ሱዳንን ድንበር በተመለከተ የተለያዩ የውጭ የዜና ማሰራጫዎችና የግል ሚዲያዎች ያስተላለፉት ዘገባ ከዕውነት የራቀና የሁለቱን ሀገራት ሰላም ለማናጋት የተቀነባበረ መሆኑን የቤኒሻንጉል ክልል ርዕሰ መስተዳደር አቶ ያረጋል አይሸሹም አስታወቁ።

    ርዕሰ መስተዳድሩ አቶ ያረጋል አይሸሹም ዛሬ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ላይ እንዳስታወቁት፤ሁለቱ ሀገራት በሚዋሰኑበት ድንበር አካባቢ እስካሁን ምንም አይነት ችግር ሳይከሰት ተባብረውና ተደጋግፈው እየኖሩ ነው።

    የአሜሪካና የጀርመን ድምጽ ሬድዮ አገልገሎቶችና ሌሎች ሚዲያዎች ኢትዮጵያ ለሱዳን መሬት ቆርሳ ሸጣለች በማለት ሰሞኑን የሚያናፍሱት ወሬ የሁለቱን አገሮች ሰላም ለማደናቀፍ ካልሆነ በስቀር እውነትነት እንደሌለው አስረድተዋል።

    የድንበር ጉዳይን በተመለከተ የድንበር ማካለል ኮሚሽኑ ከተለያዩ አካላት ጋር በመሆን ጥናት ከመጀመሩ በስተቀር ወደ ድንበር ማካለል ገና አለመግባቱን ያስታወቁት አቶ ያረጋል፤ ድንበሩ ተካሎ እንዳለቀና ከኢትዮጵያ ተቆርጦ ለሱዳን እንደተሰጠ ተደርጎ በዜና ማሰራጫዎች መቅረቡ የሙያ ስነ ምግባርን የሚጥስና የሁለቱን ሀገራት ህዝቦች ወደ አላስፈላጊ ብጥብጥ እንዲገቡ የሚጋብዝ ነው ብለዋል።

    የሁለቱ ሀገሮች ህዝቦች በአሁኑ ወቅት ከድህነት ለመውጣት ሰፊ እንቅስቃሴ እያደረጉና በድንበር አካባቢ ያለው ህብረተሰብ በሰላም ኑሮውን እየገፋ እንደሚገኝ ጠቁመው፤ የሚነዛውን ወሬ ወደጎን በመተው የጀመረውን ልማት አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ተናግረዋል።

    የድንበር ማካለል ሂደቱ ዓለም አቀፍ መርህን በተከተለና ፍጹም ሰላም በሰፈነበት ሁኔታ የሚካሄድ መሆኑን ያረጋገጡት አቶ ያረጋል፤ጠባብ የፖለቲካ ድርጅቶችና የእነሱን ወሬ የሚያናፍሱ ሚዲያዎች ከድርጊታቸው ሊቆጠቡ እንደሚገባ አሳስበዋል።

    በተመሳሳይ በቤኒሻንጉል ክልል ጠረፋማ አካባቢዎች ሻዕቢያና የሻዕቢያ ቅጥረኞች ከሚያዚያ ወር ጀምሮ በክልሉ በተለያዩ ጠረፋማ አካባቢዎች የህዝቡን ሰላም ለማናጋት ፈጥረውት የነበረው ጸረ ሰላም እንቅስቃሴ በቁጥጥር ስር እንደዋለ መናገራቸውን ዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል ዘግቧል።

WALTA INFORMATION CENTER, AMHARIC NEWS

  • Permalink for 'WALTA_INFORMATION_CENTER__AMHARIC_NEWS/2008/05/17/%e1%8b%a8%e1%8a%a2%e1%89%b5%e1%8b%ae_%e1%88%b1%e1%8b%b3%e1%8a%95%e1%8a%95_%e1%8b%b5%e1%8a%95%e1%89%a0%e1%88%ad_%e1%89%a0%e1%89%b0%e1%88%98%e1%88%88%e1%8a%a8%e1%89%b0_%e1%88%9a%e1%8b%b2%e1%8b%ab%e1%8b%8e%e1%89%bd_%e1%8b%ab%e1%88%b5%e1%89%b0%e1%88%8b%e1%88%88%e1%8d%89%e1%89%b5_%e1%8b%98%e1%8c%88%e1%89%a3_%e1%8a%a8%e1%8b%95%e1%8b%8d%e1%8a%90%e1%89%b5_%e1%8b%a8%e1%88%ab%e1%89%80_%e1%88%98%e1%88%86%e1%8a%91_%e1%89%b0%e1%8c%88%e1%88%88%e1%8d%80'

    የኢትዮ ሱዳንን ድንበር በተመለከተ ሚዲያዎች ያስተላለፉት ዘገባ ከዕውነት የራቀ መሆኑ ተገለፀ

    Posted: May 17th, 2008, 9:07am EDT
    አዲስ አበባ ግንቦት 7/2000/ዋኢማ/የኢትዮ ሱዳንን ድንበር በተመለከተ የተለያዩ የውጭ የዜና ማሰራጫዎችና የግል ሚዲያዎች ያስተላለፉት ዘገባ ከዕውነት የራቀና የሁለቱን ሀገራት ሰላም ለማናጋት የተቀነባበረ መሆኑን የቤኒሻንጉል ክልል ርዕሰ መስተዳደር አቶ ያረጋል አይሸሹም አስታወቁ።

    ርዕሰ መስተዳድሩ አቶ ያረጋል አይሸሹም ዛሬ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ላይ እንዳስታወቁት፤ሁለቱ ሀገራት በሚዋሰኑበት ድንበር አካባቢ እስካሁን ምንም አይነት ችግር ሳይከሰት ተባብረውና ተደጋግፈው እየኖሩ ነው።

    የአሜሪካና የጀርመን ድምጽ ሬድዮ አገልገሎቶችና ሌሎች ሚዲያዎች ኢትዮጵያ ለሱዳን መሬት ቆርሳ ሸጣለች በማለት ሰሞኑን የሚያናፍሱት ወሬ የሁለቱን አገሮች ሰላም ለማደናቀፍ ካልሆነ በስቀር እውነትነት እንደሌለው አስረድተዋል።

    የድንበር ጉዳይን በተመለከተ የድንበር ማካለል ኮሚሽኑ ከተለያዩ አካላት ጋር በመሆን ጥናት ከመጀመሩ በስተቀር ወደ ድንበር ማካለል ገና አለመግባቱን ያስታወቁት አቶ ያረጋል፤ ድንበሩ ተካሎ እንዳለቀና ከኢትዮጵያ ተቆርጦ ለሱዳን እንደተሰጠ ተደርጎ በዜና ማሰራጫዎች መቅረቡ የሙያ ስነ ምግባርን የሚጥስና የሁለቱን ሀገራት ህዝቦች ወደ አላስፈላጊ ብጥብጥ እንዲገቡ የሚጋብዝ ነው ብለዋል።

    የሁለቱ ሀገሮች ህዝቦች በአሁኑ ወቅት ከድህነት ለመውጣት ሰፊ እንቅስቃሴ እያደረጉና በድንበር አካባቢ ያለው ህብረተሰብ በሰላም ኑሮውን እየገፋ እንደሚገኝ ጠቁመው፤ የሚነዛውን ወሬ ወደጎን በመተው የጀመረውን ልማት አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ተናግረዋል።

    የድንበር ማካለል ሂደቱ ዓለም አቀፍ መርህን በተከተለና ፍጹም ሰላም በሰፈነበት ሁኔታ የሚካሄድ መሆኑን ያረጋገጡት አቶ ያረጋል፤ጠባብ የፖለቲካ ድርጅቶችና የእነሱን ወሬ የሚያናፍሱ ሚዲያዎች ከድርጊታቸው ሊቆጠቡ እንደሚገባ አሳስበዋል።

    በተመሳሳይ በቤኒሻንጉል ክልል ጠረፋማ አካባቢዎች ሻዕቢያና የሻዕቢያ ቅጥረኞች ከሚያዚያ ወር ጀምሮ በክልሉ በተለያዩ ጠረፋማ አካባቢዎች የህዝቡን ሰላም ለማናጋት ፈጥረውት የነበረው ጸረ ሰላም እንቅስቃሴ በቁጥጥር ስር እንደዋለ መናገራቸውን ዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል ዘግቧል።

Amharic News, Ethiopian News, ECTV Zena

  • Permalink for 'Amharic_News__Ethiopian_News__ECTV_Zena/2008/02/15/%e1%89%a0%e1%8b%8d%e1%8c%ad_%e1%8b%a8%e1%88%9a%e1%8a%96%e1%88%a9_%e1%8b%a8%e1%8b%b5%e1%88%ac%e1%8b%b0%e1%8b%8b_%e1%89%b0%e1%8b%88%e1%88%8b%e1%8c%86%e1%89%bd%e1%8a%93_%e1%8b%88%e1%8b%b3%e1%8c%86%e1%89%bd_%e1%8b%a8%e1%88%86%e1%8a%91_%e1%8a%a2%e1%89%b5%e1%8b%ae%e1%8c%b5%e1%8b%ab%e1%8b%8d%e1%8b%ab%e1%8a%95_%e1%89%a0%e1%8b%b5%e1%88%ac%e1%8b%b0%e1%8b%8b_%e1%8a%a2%e1%8a%95%e1%89%a8%e1%88%b5%e1%89%b5_%e1%88%9b%e1%8b%b5%e1%88%a8%e1%8c%8d_%e1%8c%80%e1%88%98%e1%88%a9'

    በውጭ የሚኖሩ የድሬደዋ ተወላጆችና ወዳጆች የሆኑ ኢትዮጵያውያን በድሬደዋ ኢንቨስት ማድረግ ጀመሩ

    Posted: February 15th, 2008, 6:22am EST
    ድሬዳዋ ጥር 19/2000/ዋኢማ/ በውጭ የሚኖሩ የድሬዳዋ ተወላጆችና ወዳጆች በከተማዋ በተለያዩ የኢንቨስትመንት ዘርፎች መሰማራት ጀመሩ። በሚሊኒየሙ ወደ ሀገራቸው የተመለሱ አንደንድ ኢትዮጵያዊያን ፈቃድ ወስደው የቁም እንስሳትን ወደ ውጭ በመላክ ንግድ መሠማራታቸውን አስታወቁ።

    በአውሮፓ፣ በአሜሪካ፣ በእስያና በአውስትራሊያ የሚኖሩ የድሬደዋ ተወላጆች ለዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል በሰጡት አስተያየት በሚሊኒየሙ በተፈጠረው መነቃቃት በከተማዋ ኢንቨስትመንት ለመሰማራት አነሳስቷቸዋል።

WALTA INFORMATION CENTER, AMHARIC NEWS

  • Permalink for 'WALTA_INFORMATION_CENTER__AMHARIC_NEWS/2008/01/29/%e1%89%a0%e1%8b%8d%e1%8c%ad_%e1%8b%a8%e1%88%9a%e1%8a%96%e1%88%a9_%e1%8b%a8%e1%8b%b5%e1%88%ac%e1%8b%b0%e1%8b%8b_%e1%89%b0%e1%8b%88%e1%88%8b%e1%8c%86%e1%89%bd%e1%8a%93_%e1%8b%88%e1%8b%b3%e1%8c%86%e1%89%bd_%e1%8b%a8%e1%88%86%e1%8a%91_%e1%8a%a2%e1%89%b5%e1%8b%ae%e1%8c%b5%e1%8b%ab%e1%8b%8d%e1%8b%ab%e1%8a%95_%e1%89%a0%e1%8b%b5%e1%88%ac%e1%8b%b0%e1%8b%8b_%e1%8a%a2%e1%8a%95%e1%89%a8%e1%88%b5%e1%89%b5_%e1%88%9b%e1%8b%b5%e1%88%a8%e1%8c%8d_%e1%8c%80%e1%88%98%e1%88%a9'

    በውጭ የሚኖሩ የድሬደዋ ተወላጆችና ወዳጆች የሆኑ ኢትዮጵያውያን በድሬደዋ ኢንቨስት ማድረግ ጀመሩ

    Posted: January 29th, 2008, 10:08am EST
    ድሬዳዋ ጥር 19/2000/ዋኢማ/ በውጭ የሚኖሩ የድሬዳዋ ተወላጆችና ወዳጆች በከተማዋ በተለያዩ የኢንቨስትመንት ዘርፎች መሰማራት ጀመሩ። በሚሊኒየሙ ወደ ሀገራቸው የተመለሱ አንደንድ ኢትዮጵያዊያን ፈቃድ ወስደው የቁም እንስሳትን ወደ ውጭ በመላክ ንግድ መሠማራታቸውን አስታወቁ።

    በአውሮፓ፣ በአሜሪካ፣ በእስያና በአውስትራሊያ የሚኖሩ የድሬደዋ ተወላጆች ለዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል በሰጡት አስተያየት በሚሊኒየሙ በተፈጠረው መነቃቃት በከተማዋ ኢንቨስትመንት ለመሰማራት አነሳስቷቸዋል።

Amharic News, Ethiopian News, ECTV Zena

  • Permalink for 'Amharic_News__Ethiopian_News__ECTV_Zena/2008/01/29/%e1%8b%b5%e1%88%ad%e1%8c%85%e1%89%b6%e1%89%b9_%e1%88%88%e1%88%9d%e1%88%ad%e1%8c%ab%e1%8b%8d_%e1%8a%a855%e1%88%ba_%e1%89%a0%e1%88%8b%e1%8b%ad_%e1%8b%95%e1%8c%a9%e1%8b%8e%e1%89%bd_%e1%88%9b%e1%89%85%e1%88%a8%e1%89%a3%e1%89%b8%e1%8b%8d%e1%8a%95_%e1%8c%88%e1%88%88%e1%8c%b9'

    ድርጅቶቹ ለምርጫው ከ55ሺ በላይ ዕጩዎች ማቅረባቸውን ገለጹ

    Posted: January 29th, 2008, 10:07am EST
    አክሱም ጥር 19/2000/ዋኢማ/ በትግራይ ማዕከላዊ ዞን በመጪው ሚያዚያ ወር በሚካሄደው የአካባቢና ማሟያ ምርጫ ህወሐትን ወክለው የሚወዳደሩ 49ሺ 516 ዕጩ ተወዳዳሪዎች በሕዝብ መገምገማቸውን የዞኑ የህዝብ አደረጃጀት ኃላፊ ገለጹ። የብሔረ አማራ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ /ብአዴን/ ለባህር ዳር ከተማ ያዘጋጃቸውን 6ሺ ዕጩዎች በህዝብ እያስገመገመ ነው።

WALTA INFORMATION CENTER, AMHARIC NEWS

  • Permalink for 'WALTA_INFORMATION_CENTER__AMHARIC_NEWS/2008/01/29/%e1%8b%b5%e1%88%ad%e1%8c%85%e1%89%b6%e1%89%b9_%e1%88%88%e1%88%9d%e1%88%ad%e1%8c%ab%e1%8b%8d_%e1%8a%a855%e1%88%ba_%e1%89%a0%e1%88%8b%e1%8b%ad_%e1%8b%95%e1%8c%a9%e1%8b%8e%e1%89%bd_%e1%88%9b%e1%89%85%e1%88%a8%e1%89%a3%e1%89%b8%e1%8b%8d%e1%8a%95_%e1%8c%88%e1%88%88%e1%8c%b9'

    ድርጅቶቹ ለምርጫው ከ55ሺ በላይ ዕጩዎች ማቅረባቸውን ገለጹ

    Posted: January 29th, 2008, 10:07am EST
    አክሱም ጥር 19/2000/ዋኢማ/ በትግራይ ማዕከላዊ ዞን በመጪው ሚያዚያ ወር በሚካሄደው የአካባቢና ማሟያ ምርጫ ህወሐትን ወክለው የሚወዳደሩ 49ሺ 516 ዕጩ ተወዳዳሪዎች በሕዝብ መገምገማቸውን የዞኑ የህዝብ አደረጃጀት ኃላፊ ገለጹ። የብሔረ አማራ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ /ብአዴን/ ለባህር ዳር ከተማ ያዘጋጃቸውን 6ሺ ዕጩዎች በህዝብ እያስገመገመ ነው።

Amharic News, Ethiopian News, ECTV Zena

  • Permalink for 'Amharic_News__Ethiopian_News__ECTV_Zena/2008/01/29/%e1%89%a0%e1%8a%a8%e1%89%b0%e1%88%9e%e1%89%bd_%e1%89%a01_%e1%8a%90%e1%8c%a5%e1%89%a53_%e1%89%a2%e1%88%8a%e1%8b%ae%e1%8a%95_%e1%89%a5%e1%88%ad_%e1%8b%88%e1%8c%ad_%e1%8b%a8%e1%8c%8b%e1%88%ab_%e1%88%98%e1%8a%96%e1%88%aa%e1%8b%ab_%e1%89%a4%e1%89%b6%e1%89%bd_%e1%8c%8d%e1%8a%95%e1%89%a3%e1%89%b3_%e1%8a%a5%e1%8b%a8%e1%89%b0%e1%8a%ab%e1%88%84%e1%8b%b0_%e1%8a%90%e1%8b%8d'

    በከተሞች በ1 ነጥብ3 ቢሊዮን ብር ወጭ የጋራ መኖሪያ ቤቶች ግንባታ እየተካሄደ ነው

    Posted: January 29th, 2008, 10:05am EST
    አዲስ አበባ ጥር 19/2000/ አዲስ አበባና ድሬደዋ አስተዳደሮችን ጨምሮ በሰባት ክልሎች በከተሞች አካባቢ የሚታየውን የመኖሪያ ቤት እጥረት ለማቃለል በ1 ነጥብ 3 ቢሊየን ብር ወጭ የጋራ መኖሪያ ቤቶች ግንባታ እያሄካደ መሆኑን የሥራና ከተማ ልማት ሚኒስቴር አስታወቀ።

    ሚኒስትሩ በየክልሎቹ እየተካሄደ ያለውን የቤቶች ልማት ፕሮግራም የግማሽ ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ለመገምገም ዛሬ ባዘጋጀው የውይይት መድረክ ላይ ባቀረበው ሪፖርት እንዳስታወቀው፤ በግማሽ ዓመት ውስጥ የግንባታ ስራቸውን ለመጀመር ከታቀዱት 2ሺ 855 የጋራ መኖሪያ ህንፃዎች መካከል የ2ሺ 290 ህንፃዎች ግንባታቸው ተጀምሯል።

WALTA INFORMATION CENTER, AMHARIC NEWS

  • Permalink for 'WALTA_INFORMATION_CENTER__AMHARIC_NEWS/2008/01/29/%e1%89%a0%e1%8a%a8%e1%89%b0%e1%88%9e%e1%89%bd_%e1%89%a01_%e1%8a%90%e1%8c%a5%e1%89%a53_%e1%89%a2%e1%88%8a%e1%8b%ae%e1%8a%95_%e1%89%a5%e1%88%ad_%e1%8b%88%e1%8c%ad_%e1%8b%a8%e1%8c%8b%e1%88%ab_%e1%88%98%e1%8a%96%e1%88%aa%e1%8b%ab_%e1%89%a4%e1%89%b6%e1%89%bd_%e1%8c%8d%e1%8a%95%e1%89%a3%e1%89%b3_%e1%8a%a5%e1%8b%a8%e1%89%b0%e1%8a%ab%e1%88%84%e1%8b%b0_%e1%8a%90%e1%8b%8d'

    በከተሞች በ1 ነጥብ3 ቢሊዮን ብር ወጭ የጋራ መኖሪያ ቤቶች ግንባታ እየተካሄደ ነው

    Posted: January 29th, 2008, 10:05am EST
    አዲስ አበባ ጥር 19/2000/ አዲስ አበባና ድሬደዋ አስተዳደሮችን ጨምሮ በሰባት ክልሎች በከተሞች አካባቢ የሚታየውን የመኖሪያ ቤት እጥረት ለማቃለል በ1 ነጥብ 3 ቢሊየን ብር ወጭ የጋራ መኖሪያ ቤቶች ግንባታ እያሄካደ መሆኑን የሥራና ከተማ ልማት ሚኒስቴር አስታወቀ።

    ሚኒስትሩ በየክልሎቹ እየተካሄደ ያለውን የቤቶች ልማት ፕሮግራም የግማሽ ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ለመገምገም ዛሬ ባዘጋጀው የውይይት መድረክ ላይ ባቀረበው ሪፖርት እንዳስታወቀው፤ በግማሽ ዓመት ውስጥ የግንባታ ስራቸውን ለመጀመር ከታቀዱት 2ሺ 855 የጋራ መኖሪያ ህንፃዎች መካከል የ2ሺ 290 ህንፃዎች ግንባታቸው ተጀምሯል።

Ethiopian News Agency (ENA) Amharic News

  • Permalink for 'Ethiopian_News_Agency__ENA__Amharic_News/2007/09/06/%e1%8b%a8%e1%88%9a%e1%88%8c%e1%8a%92%e1%8b%a8%e1%88%99%e1%8a%95_%e1%89%a0%e1%8a%a0%e1%88%8d_%e1%88%88%e1%88%9b%e1%8a%ad%e1%89%a0%e1%88%ad_%e1%8a%a8%e1%89%b0%e1%88%88%e1%8b%ab%e1%8b%a9_%e1%8a%a0%e1%88%88%e1%88%9b%e1%89%b5_%e1%88%88%e1%88%98%e1%8c%a1_%e1%8a%a5%e1%8a%95%e1%8c%8d%e1%8b%b6%e1%89%bd_%e1%8b%b0%e1%88%9b%e1%89%85_%e1%8a%a0%e1%89%80%e1%89%a3%e1%89%a0%e1%88%8d_%e1%89%b0%e1%8b%b0%e1%88%a8%e1%8c%88'

    የሚሌኒየሙን በአል ለማክበር ከተለያዩ አለማት ለመጡ እንግዶች ደማቅ አቀባበል ተደረገ

    Posted: September 6th, 2007, 8:19am EDT
    አዲስ አበባ, ነሐሴ 30 ቀን 1999 (አዲስ አበባ) - አዲሱን የኢትዮጵያ ሚሌኒየም በአል ለማክበር ከተለያዩ አለማት ከ500 በላይ ኢትዮጵያውያን፣ ትውልድ ኢትዮጵያውያንና የውጭ አገራት ዜጎች ትናንት ማምሻውን አዲስ አበባ ገብተዋል፡፡
    ለእንግዶቹ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ የፈረሙበት የእንኳን ደህና መጣችሁ የመልካም ምኞች መግለጫ ካርድና አበባ ተበርክቶ
  • Permalink for 'Ethiopian_News_Agency__ENA__Amharic_News/2007/09/06/%e1%8a%a2%e1%89%b5%e1%8b%ae%e1%8c%b5%e1%8b%ab_%e1%8b%8d%e1%88%b5%e1%8c%a5_%e1%8a%a0%e1%89%85%e1%8c%a3%e1%8c%ab%e1%8a%95_%e1%8b%a8%e1%88%9a%e1%8c%a0%e1%89%81%e1%88%9d_%e1%8b%a8%e1%88%98%e1%88%a8%e1%8c%83_%e1%8a%a0%e1%8c%88%e1%88%8d%e1%8c%8d%e1%88%8e%e1%89%b5_%e1%89%b4%e1%8a%ad%e1%8a%96%e1%88%8e%e1%8c%82_%e1%8b%ad%e1%8d%8b_%e1%88%86%e1%8a%90'

    ኢትዮጵያ ውስጥ አቅጣጫን የሚጠቁም የመረጃ አገልግሎት ቴክኖሎጂ ይፋ ሆነ

    Posted: September 6th, 2007, 8:17am EDT
    አዲስ አበባ, ጳጉሜን 1 ቀን 1999 (አዲስ አበባ) - ኢትዮጵያ ውስጥ ለተጓዦችና ለአገር ጎብኝዎች አቅጣጫዎችን በመጠቆም የመረጃ አገልገሎት የሚሰጥ ''ግሎባል ፖዚሽ ሶሉሽን'' /ጂፒኤስ/ የተባለ አዲስ ቴክኖሎጂ ተግባራዊ ሊሆን ነው፡፡ 27 ሺህ መንደሮችን፣ ከተሞችንና ወረዳዎችንና ያካተተ መሆኑን የፈጠራው ባለቤት ገለጹ፡፡
    ይህንኑ ቴክኖሎጂ በሸራተን አዲስ በተግባር ሲሞከር የቱሪዝምና የባህል ሚኒስተሩ አምባሳደር ሙሐመድ ዲሪር እንደገለጹት የዚህ አይነቱ ዘመናዊ የመረጃ ቴክኖሎጂ ኢትዮጵያ ውስጥ ተግባራዊ መሆኑለቱሪስቶች ጠቃሚ ነው ፡፡

Amharic News

  • Permalink for 'Amharic_News/2007/02/18/'

    [nt]

    Posted: February 18th, 2007, 9:14am EST
  • Permalink for 'Amharic_News/2007/02/16/%e1%89%a0%e1%8b%88%e1%8b%ab%e1%8a%94_%e1%8a%a2%e1%88%85%e1%8a%a0%e1%8b%b4%e1%8c%8d_%e1%8b%a8%e1%8c%8d%e1%8b%b5%e1%8b%ab_%e1%89%b5%e1%8a%a5%e1%8b%9b%e1%8b%9d_%e1%89%a0%e1%8c%8d%e1%8d%8d_%e1%8b%b0%e1%88%9b%e1%89%b8%e1%8b%8d_%e1%89%a0%e1%8d%88%e1%88%b0%e1%88%b0_%e1%8b%88%e1%8c%88%e1%8a%96%e1%89%bd_%e1%88%98%e1%89%83%e1%89%a5%e1%88%ad_%e1%88%8b%e1%8b%ad_%e1%88%88%e1%88%98%e1%8c%a8%e1%8d%88%e1%88%ad_%e1%88%88%e1%8b%88%e1%8b%ab%e1%8a%94_%e1%88%9a%e1%88%8a%e1%8a%92%e1%8b%a8%e1%88%9d_%e1%8b%a8%e1%89%b0%e1%8c%8b%e1%89%a0%e1%8b%99_%e1%8b%9c%e1%8c%8e%e1%89%bd_%e1%8c%89%e1%8b%b3%e1%8b%ad_%e1%8a%a5%e1%8b%ab%e1%88%b0%e1%8c%8b_%e1%88%98%e1%88%86%e1%8a%91_%e1%89%b3%e1%8b%88%e1%89%80'

    በወያኔ ኢህአዴግ የግድያ ትእዛዝ በግፍ ደማቸው በፈሰሰ ወገኖች መቃብር ላይ ለመጨፈር ለወያኔ ሚሊኒየም የተጋበዙ ዜጎች ጉዳይ እያሰጋ መሆኑ ታወቀ

    Posted: February 16th, 2007, 7:56am EST

    አዲስ አበቤው ተመዝግቦ የከፈለበትን የኮንዶሚንየም ቤት ተነጥቆ
    እነስዩም በረደድ ሊያከራዩት መሆኑ ተደረሰበት

    በ1997 ዓ.ም. ተካሂዶ የነበረውን አገር አቀፍ ምርጫ ምክንያት በማድረግ ቅስቀሳ ሲደረግ የአብዛኛውን ወገን ድጋፍ ለማግኘት ይረዳኛል ብሎ ያሰበው ወያኔ ኢህአዴግ ላታለያነት ተጠቅሞበት የነበረውን «የመኖሪያ ቤት ችግር እቀርፋለሁ» የሚለው ስብከቱ በምርጫ መሸነፉን ካወቀ ወዲህ ቃሉን ለማጠፍ መገደዱንና አሁንም የቅድሚያ ክፍያቸውን ለከፈሉ ዜጎች ሳይሰጥ ለራሱ መታያና የፕሮፓጋንዳ ትርፍ መሰብሰቢያ ሊያደርገው መሆኑን ምንጮቻችን ዘገቡ
    በወያኔ ኢህአዴግ አፍቃሪነታቸውና ሙዋቹን ክንፈ ገብረ መድህንን የተከካው የደህንነት ባለስልጣን አቶ ጌታቸው የስጋ ዘመድ የሆነው ስዩም በረደድ እና በተቃያያሪ አመሉ የሚታወቀው ሙሉጌታ አስራተካሳ የሚመራው የሚሊኒየም አከባበር ብሄራዊ ኮሚቴ በአዲስ አበባ ድሃ ህዝብ ስም የተሰሩ የኮንዶምኒየም ቤቶችን ከግፈኞች እና ከአምባገነን ገዳዮች ጋር አጨብጭቦ ለማክበር ወደ ኢትዮጵያ የሚመጡትን እንግዶች መቀበያና ማስተናገጃ ሊያደርገው መሆኑን ታማኝ ውስጥ አዋቂዎችን በመጥቀስ ምንጮቻችን ዘግበዋል
    ለአዲስ አበባ መስተዳድርና ለአዲስ አበባ የቤቶች ኤጀንሲ ቅርብ የሆኑት እነዚሁ ታማኝ ውስጥ አዋቂዎች በወያኔ ኢህአዴግ የግድያ ትእዛዝ በግፍ ደማቸው በፈሰሰ ወገኖች መቃብር ላይ ለመረማመድ እና ለመጨፈር የተጋበዙ እንዲያርፉበት ተብሎ ከእለት ጉሮሮው እየቀነሰ በችግር ተቆራምዶ ቅድሚያ ክፍያ የከፈለበትን የኮንዶሚንየም ቤት የሚያጣው የአዲስ አበባ ነዋሪ «ለምን᐀» ብሎ ጥያቄ እንዳያነሳ ቤቱ የሚሰጠው በእጣ ስለሆነ እጣው አልወጣም ጥሪ እስኪደረግላችሁ ተጠባበቁ የሚል መልስ እንዲሰጥ በቤቶች ኤጀንሲ በኩል መወሰኑን እናውቃለን ሲሉ አስረድተዋል
    እየገደሉ እያፈኑ እና በጅምላ እያሰሩ የስልጣን እድሜውን አራዝሞ መኖር ለመረጠ ፋሽስት ጋር ተባባሪ ሆኖ በድሃው ህዝብ ላይ መደለል አሳዛኝ ነው የሚሉ የጉዳዩ ተመልካቾች ነዋሪውም ቢሆን እኮ የወያኔ አጨብጫቢዎችና አሸርጋጆች የሚያከብሩት ሚሊኒየም አድማቂ ሳይሆን በግፍ የተሰዉ የዲሞክራሲ ሰማእታት መንፈስ እንዳይፋረደው ራሱን ቢያገልም እንደ ማንኛውም አዲስ አመት በአዲስ ቤት መኖር አይጠላበትም ግን የኢህአዴግ ቱባ ባለስልጣናት ከህዝብ ጥቅም የራሳቸው ጥቅም ስለሚበልጥባቸው ይህን እርምጃ ለመውሰድ ተገድደዋል በማለት መናገራቸው በዘገባው ተመልክቶዋል
    በበላይነት ስዩም መስፍን የሚመሩትና በእነስዩም በረደድ እና ሙሉጌታ አስራተ ናሳ አማንኝነት ሊካሄድ የታቀደው የወያኔ ሚሊኒየም በአል ለማክበር ይገኛሉ ከእኛ ጋር ያጨበጭባሉ ተብለው የተገመቱት ወገኖች ህሊና ሳይኖራቸው ቀርቶ ቢመጡ ሊያርፉበት የሚችሉትን ቤት ያለ ህዝብ ፍላጎት በአዲስ አበባ ህዝብ ትከሻ ላይ መቀመጥ የመረጡት የሞግዚቱ አስተዳደር ብርሃነ ዴሬሳ ፊርማ ወጪ የተደረገ ደብዳቤ ለከተማው ቤቶች ኤጀንሲ እንዲደርስ መደረጉ ታውቆዋል
    በዚህም መሰረት ይህ ኢህአዴጋውያን የተጠራቀሙበት ኮሚነ የኮንዶሚኒየም ሕንፃዎችን ለመጠቀም ተፈቅዶለታል ሲሉ ምንጮቻችን ዘግበዋል
    በዚሁ የወያኔ ሚሊኒየም በዓል እስከ 300 ሺህ የሚገመቱ እንግዶች ይመጣሉ የሚሉት እነስዩም በረደድ የግንቦቱን ምርጫ ተከትሎ ወያኔ ሰላማዊ ዜጎችን ሲገድል በእንባ እየተራጩ ወገኔ አለቀ አስጥሉልኝ ብለው ምእራባውያንና አውሮፓውያንን የተማጸኑ ዜጎች በወቅቱ የተቀረጸ ምስላቸው የተቃውሞ ድበጻቸውን ካሰሙበት አገር ከሚገኝ ኤምባሲ በወያኔ ኢህአዴግ ጉዳይ አስፈጻሚዎቸር ተቀነባብሮ አዲስ አበባ ለሚገኘው የውጭ ጉዳይ ሚኒስነር መስሪያቤት መላኩንና የሚኒስነር መስሪያቤቱ የተለያዩ ክፍሎችና ዳይሬክቶሬቶች ውስጥ ያሉ የኢህአዴግ ታማኝ አገልጋዮች «እገሌ ፤ እገሌ» እያሉ በመምረጥ ላይ መሆናቸው ለማወቅተችሎዋል
    ይህ የሚያገለግለው የሰው ዘር ማየት ያስጠላው ወያኔ ኢህአዴግ በአል ብለው የሚመጡ እንግዶችን ከቦሌ አየር ማረፊያ የእግረ ሙቅ በማጥለቅ አቀባበል ሊያደርግላቸው በማሰቡ መሆኑን ከዚሁ ጋር በተያያዘ ስራ የበዛባቸው የደህንነት ተቁዋሙ ባልደረቦች መናገራቸው በዘገባው ተመልክቶዋል
    ለበዓሉ የሚመጡትን እንግዶች ከሆቴሎች ሌላ ሌሎች ማረፊያ ቦታዎችን ለማመቻቸት ከሚያስችለው ዝግጅት አንዱ የሆነውን ኮንዶሚኒየም ቤቶች ተመዝግቦና ገንዘቡን ከፍሎ እረከባለሁ በማለት ከሚጠባበቀው ህዝብ በመንጠቅ ለመስጠት ስምምነት ላይ መደረሱን የሰሙ ወገኖች ጥራት የጎደለው እና በመሰነጣጠቅ ገና ከጅምሩ የማስመሰያ ግንባታ እንደነበረ ህዝቡ አውቆታል ከዚሁ ብሶ በሸፍጥ ለሌላ በማዛወር ገንዘብ ለማግበስበስ መሞከር አልጠግብ ባይነት ነው ሲሉ የወያኔ ኢህአዴግ ቱባ ባለስልጣናትን በሆዳቸው መሸነፍ አስመልክተው መተቸታቸው በዘገባው ተመልክቶዋል
    እነስዩም በረደድ በበዓሉ ዋዜማ ዓመቱን በመሉ ሊመጡ የሚችሉ እንግዶችን በአዲስ አበባ ከተማ በመጠናቀቅ ላይ ያሉ ኮንዶሚንየም ቤቶችውስጥ እንዲያርፉ በማድረግ የገቢ ምንጭ የሚሆኑበት መንገድ ተሰልቶ ስለሚገኘው ትርፍ ግምታዊ ስሌት የሚያሰላ ቡድን እንዶቁዋቁዋም ማድረጋቸውን ምንጮቻችን አስረድተዋል
    ይህ በእንዲህ እንዳለ ይህ ንን ዘገባ እያጠናቀርን ባለንበት ወቅት በተገኛ ተመሳሳይ የምንጮቻችችን ዘገባ በኮንዶሚኒየም ቤቶች ከሚያርፉ እንግዶች ሌላ በእነሱም መካከል ልዩነት በመፍጠር በኮንዶሚኒየም ለመቆየት የሚጠየቁት ክፍያ መክፈል ካልቻሉ የከፍተኛ ትምህርት ተቁዋማት ተማሪዎች ትምህርት እንዲያቆሙ ማድረግ አስቸጋሪ ነው ተብሎ ቢታሰብም ማደሪያ ክፍሎቻቸውን እንዲለቁ እና ዩኒቨርስቲዎች የመኝታ አገልግሎታቸውን ለእንግዳ ማረፊያ እንዲከራይ ሀሳብ መቅረቡን ለማወቅ ተችሎዋል
    ይህ ሃሳብ ሁለት ዋና ዋና የተባሉ ጥያዎችን አስነስተው ነበር ያሉት ምንጮቻችን አንዱ የዩኒቨርስቲ መኝታዎች የሚያስገኙትን ገቢ በባለቤትነት የሚወስደው ማንነው᐀ የሚለው ሲሆን ሁለተኛው የክፍለሃገር ተማሪዎችን በተመለከተ ወዴት ማዘዋወር ይቻላል᐀ የሚለውን ከሌሎች ጥያቄዎች ጋር አዛምዶ መልስ ለመፈለግ ጉዳዩ ይጠና መባሉን ከታማኝ ውስጥ አዋቂ ለማረጋገጥ ችለናል ሲሉ ዘግበዋል

  • Permalink for 'Amharic_News/2007/02/16/%e1%8a%90%e1%8c%bb_%e1%8a%90%e1%8b%8d_%e1%8a%a5%e1%8b%a8%e1%89%b0%e1%89%a3%e1%88%88_%e1%8b%a8%e1%88%9a%e1%88%88%e1%8d%88%e1%8d%8d%e1%88%88%e1%89%b5_%e1%8d%8d%e1%88%ad%e1%8b%b5_%e1%89%a4%e1%89%b5_%e1%89%a0%e1%8a%a2%e1%88%85%e1%8b%b4%e1%8c%8d_%e1%89%b3%e1%88%9b%e1%8a%9d_%e1%8a%a0%e1%8c%88%e1%88%8d%e1%8c%8b%e1%8b%ae%e1%89%bd_%e1%8b%a8%e1%8a%a5%e1%8c%85_%e1%88%98%e1%8b%b3%e1%8d%8d_%e1%88%8b%e1%8b%ad_%e1%8b%ab%e1%88%88_%e1%88%98%e1%88%86%e1%8a%91%e1%8a%95_%e1%8b%a8%e1%88%9a%e1%8b%ab%e1%88%98%e1%88%8b%e1%8a%ad%e1%89%b5_%e1%8a%90%e1%8b%8d_%e1%88%b2%e1%88%89_%e1%8a%a0%e1%8a%95%e1%8b%b5_%e1%8b%a8%e1%88%85%e1%8c%8d_%e1%89%a3%e1%88%88%e1%88%99%e1%8b%ab_%e1%89%b0%e1%8a%93%e1%8c%88%e1%88%a9'

    ነጻ ነው እየተባለ የሚለፈፍለት ፍርድ ቤት በኢህዴግ ታማኝ አገልጋዮች የእጅ መዳፍ ላይ ያለ መሆኑን የሚያመላክት ነው ሲሉ አንድ የህግ ባለሙያ ተናገሩ

    Posted: February 16th, 2007, 7:56am EST

    በግቦት ወር 1997 ዓ.ም. በተደረገው ምርጫ ከፍተኛ የህዝብ ድጋፍ በማግኘት ከንቲባው እንዲሆኑለት ህዝቡ የመረጣቸውን ከንቲባ ዶክተር ብርሃኑ ነጋን ወህኒ እንሰዲገቡ ያደረገው ወያኔ ኢህአዴግ ያለ ህዝብ ድጋፍ የሞግዚት አስተዳደር አድርጎ የመደባቸው ብርሃኑ ዴሬሳ እያወቁ የፍርደስ ቤት ውሳኔ መሻራቸው አዲስ አበባ የሚገኙ ምንጮች አስታወቁ
    በአዲስ አበባ ከተማ የአዲስ ከተማ ክ/ከተማ የከተማ ትርፍ ቤቶችን እንዲወረሱ ያደረገው የየካቲት 67 አዋጅ መሰረት ለረጅም ዓመታት የቀበሌ ናቸው በማለት ሲያከራክር የነበረውን ሁለት መኖሪያ ቤቶች በተመለከተ የተሰጠውን ውሳኔ ብርሃኑ ዴሬሳና የበታች ሹማምንቶቻው መሻራቸው አነጋጋ መሆኑ ታዉቆዋል
    አምና በሐምሌ ወር 1998 ዓ.ም. ለህጋዊ ወራሾች ይመለስ ሲል የተሰጠው የፍርድ ውሳኔ የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማው ሽሮታል ያሉት ምንጮች የወራሽን የባለቤትነት ማረጋገጫ ሰነድ መሰረዝ በክፍለከተማው ቀበሌ 19/20 የሚገኙ የቤት ቁጥራቸው 130 እና 131 የሆኑ በ3.000 ካሬ ሜትር ላይ የተሰሩ ቤቶች በውርስ የተላለፈላቸው እና የቤቶቹ ባለቤት ስለመሆናቸውም የሚያረጋግጥ የማረጋገጫ ደብተር ያላቸው ወራሽ ከፍርድ ቤት የተወሰነላቸውን ውሳኔ ለመሻር የሚያበቃ ስልጣን እንደሌለው የህግ ባለሙያዎች መናገራቸውን ጨምረው አስረድተዋል
    የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ በቤቶቹ ላይ የባለቤትነት መብት ሳይኖረው በማከራየት ገንዘብ ሲሰበስብ መቆየቱ እንዳለሆኖ ቤቶቹን እንዲያስረክብ ቢጠየቅም እምቢ ብሎዋል
    ከሳሽ ክሱን ሲመሰርቱ ካቀረቧቸው ማስረጃ መካከል የቤቶቹ ባለቤት ስለመሆናቸውና በውርስ መተላለፋቸውን የሚያስረዳ ከከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር በ1985 ዓም የተሰጣቸውን የባለቤትነት ማረጋገጫ ደብተር ፍ/ቤቱ በማስረጃነት በመያዝ ፍ/ቤቱ ቤቶቹን ለከሳሽ እንዲያስረክቡ በ17/11/98 ዓ.ም. በመወሰን ለክፍለ ከተማው ያስታውቃል ፡፡
    ይሁን እንጂ የፍ/ባለመብት ውሣኔው ተግባራዊ እንዳልሆነላቸው በመግለፅ ፍ/ቤቱ እንዲያስፈፅምላቸው በጠየቁት መሠረት በ10/2/99 ለአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ፖሊስ ትዕዛዝ ይሰጣል፡፡
    ቤቶቹ በፍርድ ባለእዳዎች ተይዘው ከሆነ በማስለቀቅ፣ ተቆልፈው ከሆነ በጥንቃቄ በመስበር ለፍፍርድ ባለመብት እንዲተላለፉ ለፖሊስ በትዕዛዝ ያስረዳል፡፡ ነገር ግን ይህም ተግባራዊ እንዳይሆን ክፍለ ከተማው ያግዳል የዚህ ምክንየት ደግሞ ኢህአዴግ ታማኝ ባለሙዋሎች ጌቶቻቸውን የሚያስደስት የሚመስላቸው ህዝብን በማስለቀሳቸው እንደሆነ ስለሚያምኑ መሆኑን ብዙዎች ይስማሙበታል
    የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ የኢህአዴግ ሹማምንቶች ጭራሹኑ ፍርድ ቤት የፃፈው ደብዳቤ ተቀባይነት እንደማይኖረው ለፍርድ ባለመብት እንዲያውቁት አደረገ፡፡
    በተጨማሪም የአዲስ አበባ ከተማ የመሬት ልማትና አስተዳዳር ባለስልጣን ለክፍለ ከተማው በፃፈው ደብዳቤ ቤቶቹ ኪራይ የሚከፈልባቸው የመንግስት ቤቶች መሆናቸውን የሚያስረዳ መረጃ በማዕከል እንዳለ መግለፁን ክፍለ ከተማለው ደግሞ በአዋጅ በተሰጠው ሥልጣን በሕገ ወጥ መንገድ የተሰጠን የበት ባለቤትነት ሥልጣን በሕገወጥ መንገድ የተሰጠን የቤት ባለቤትነት ማረጋገጫ ደብተር መሠረዝ የሚችል ስልጣን ስላለው የፍርድ ቤት ውሳኔ ያገኙ ባለመብቶች በእጃቸው የሚገኘውን የባለቤትነት ማረጋገጫ ደብተር እንዲመልሱ መጠየቁ የአስተዳደር ብቃት ማነስ ብቻ ሳይሆን ነጻ ነው እየተባለ የሚለፈፍለት ፍርድ ቤት በኢህዴግ ታማኝ አገልጋዮች የእጅ መዳፈ ላይ ያለ መሆኑን የሚያመላክት ነው ሲሉ አንድ የህግ ባለሙያ መናገራቸው ታውቆዋል
    ይህ ሁሉ ሲሆን በህዝብ ሳይመረጡ የተሾሙት ብርሃኑ ዴሬሳና ካቢኔያቸው ስለጉዳዩ እያወቁ ዝምታን መምረጣቸው የራሳቸውና የአባላቶቻቸው ጥቅም እስንልተነካ ድረስ ስለሌላው የህብረተሰብ ክፍል ምንም ደንታ የሌላቸው መሆኑን አስመስክሮዋል

  • Permalink for 'Amharic_News/2007/02/13/%e1%8b%a8%e1%8b%88%e1%8b%ab%e1%8a%94_%e1%8a%ab%e1%8a%95%e1%8c%8b%e1%88%ae_%e1%8d%8d%e1%88%ad%e1%8b%b5_%e1%89%a4%e1%89%b5_%e1%89%a0%e1%88%bb%e1%88%88%e1%89%83_%e1%8a%a0%e1%88%ab%e1%8c%8b%e1%8b%8d_%e1%8d%8b%e1%8b%ad%e1%88%8d_%e1%8b%a8%e1%89%b0%e1%8a%a8%e1%88%b0%e1%88%b1%e1%89%b5_%e1%8b%a8%e1%89%85%e1%8a%95%e1%8c%82%e1%89%b5_%e1%88%98%e1%88%aa%e1%8b%8e%e1%89%bd_%e1%8a%a5%e1%88%ab%e1%88%b3%e1%89%b8%e1%8b%8d%e1%8a%95_%e1%8a%a5%e1%8a%95%e1%8b%b2%e1%8a%a8%e1%88%8b%e1%8a%a8%e1%88%89_%e1%8b%88%e1%88%b0%e1%8a%90_%e1%8d%a3_%e1%89%80%e1%8c%a0%e1%88%ae%e1%8b%8d%e1%8a%95%e1%88%9d_%e1%88%88%e1%8c%8d%e1%8a%95%e1%89%a6%e1%89%b5_30_1999_%e1%8b%93.%e1%88%9d_%e1%89%80%e1%8c%a0%e1%88%a8'

    የወያኔ ካንጋሮ ፍርድ ቤት በሻለቃ አራጋው ፋይል የተከሰሱት የቅንጂት መሪዎች እራሳቸውን እንዲከላከሉ ወሰነ ፣ ቀጠሮውንም ለግንቦት 30 1999 ዓ.ም ቀጠረ

    Posted: February 13th, 2007, 10:21am EST
  • Permalink for 'Amharic_News/2007/02/12/%c2%ab%e1%8b%88%e1%8a%95%e1%8b%b1%e1%8a%95__%e1%8a%a5%e1%8c%81%e1%8a%95_%e1%8b%ad%e1%8b%98%e1%8a%95_%e1%88%b0%e1%8c%a0%e1%8a%90%e1%8b%8d%c2%bb__%e1%8a%a8%e1%89%b3%e1%88%aa%e1%8a%ad_%e1%88%9b%e1%88%85%e1%8b%b0%e1%88%ad__'

    «ወንዱን እጁን ይዘን ሰጠነው» (ከታሪክ ማህደር )

    Posted: February 12th, 2007, 6:16am EST

    በታቃዋሚነታቸው ስመጥር የሆኑ በሐገር ውስጥ የሚገኙ ድርጅቶችና ታዋቂ ግለሰቦች እንደ ጠላት የሚታዩበትና ሕልውናቸው በስጋትና በአደጋ ላይ እየወደቀ የመምጣቱን ጉዳይ ከቀን ቀን ድርጊቶች ገሐድ እያወጡት በሚጉኙበት ሒደት ላይ እንገኛለን፡፡
    በመንግስት ከፍተኛ የኃላፊነት የሥልጣን እርከን የነበሩና ታማኝነታቸው አጠራጥሮ ከነበሩበት ቦታ ዝቅ ተደርገው ከተቀመጡት ግለሰቦች ጀምሮ ሕወሓትንና በኋላም ኢህአዴግን ትናንትም ሆነ ዛሬ በመቃወም በአደባባይ እስከማውገዝ በደረሱ ግለሰቦች ሕይወት ዙሪያ የሚፈፀመው ወንጀል አሳዛኝና አስገራሚ ከመሆን አልፎ የተፈፀመባቸው የግድያ ወንጀልም ሆነ የአሟሟታቸው ጉዳይ ሁኔታዎች ከሚጠቁሙት ውጭ ይህ ነው ብሎ ለመናገር የሚያስደፍር መረጃ ማግኘት አስቸጋሪ ሆኗል፡፡
    ይባስ ብለው « ግለሰቡ እራሱን በራሱ ገደለ፡፡» ደመኛ ገደለው «ወንጀል ፈፅሞ ሲያመልጥ ተገደለ» የሚሉ እና ሌላ ሌላም ሽፋን ሲሰጣቸው ይስተዋላል፡፡ ይህ አባባል የግድያውን ስልታዊነት የሚጠቁም እንደሆነ አንዳንድ ታዛቢዎች ይናገራሉ፡፡
    በሰሜን ጎንደር የተገደለው ወጣት የሽምቅ ውጊያ መሪ አገዳደሉ የክልሉ ባለስልጣኖች እንደሚሉት «በደመኛ» ሳይሆን ሆን ተብሎ በተጠነሰሰ የባለጊዜዎች ሴራ እንደተገደለ አብዛኛው የክልሉ ነዋሪዎች ይናገራሉ፡፡
    ቀኑ ሐሙስ ነው ወሩ መፊቢት 5 ቀን ከዛሬ 14 አመት በፊት 1985 ዓ.ም. ከምሽቱ 3፡45 አካባቢ በአድርቃይ ወረዳ በዛሪማ ከተማ አሳዛኝ የግድያ ወንጀል በወጣቱ የጦር መሪ በኪዳነ ማርያም ገብረ እግዚአብሔር ላይ ተፈፀመ፡፡ በኪዳነማርያም ላይ የተፈፀመውን ግድያ አሰቃቂ የሚያደርገው በበርካታ ሽማግሌዎች ልመና በምህረት ከገባ ከአምስት ወር በኋላ በታዩት ነባራዊ ሁኔታዎች ዙሪያ በተሰላ ደባ የሞት ሰላባ መሆኑ ነው፡፡
    እንደሚታወቀው ኪዳነማርያምና የተወሰኑ ጓደኞቹ በምህረት እንዲገቡ የመንግስት ባለስልጣኖች ሽማግሌዎችን በመላክ ከፍተኛ ጥረት ካደረጉ በኋላ ከሃያ የማያንሱ ካህናትና ሸማግሌዎች የየአድባራቱን መስቀል በመያዝ አርማዛሊ ከተባለ በረሐ ዳር በአርማዶጋ ውስጥ ከሚገኙት ከእነ ኪዳነማርያም ጋር ጥር 10/1985 ዓም በመገናኘት ድርድር ተጀመረ፡፡
    ብዙም ሳይቆዩ ስምምነት ላይ ደረሱ፡፡ በዚህን ጊዜ ኪዳነና ጓደኞቹ ጦሩን ሰብስበው «በምህረት ልንገባ ነው» በማለት በተናገሩ ጊዜ ተቃውሞ ቢያጋጥማቸው ሁኔታውን ለማሳመን ሞክረው ነበር፡፡ በመጨረሻም ጦሩ «እንደሚገሏችሁ አትጠራጠሩ፡፡ እኛ ግን አንገባም፣ ደህና ሁኑ» በማለት ነበር የተሰናበታቸው ፡፡ አንዳንድ የጦሩ አባላት በኪዳነ ማርያም እግር እየወደቁ «ማማዬ ምነው ጥለኸን አትሂድ እንጂ᐀» እያሉ ቢለምኑትም የዋህ እንደሆነ የሚነገርለት ኪዳነማርያም ልቡ ጨክኖ « የሐገሬውን ሸማግሌዎችና የሐይማኖት አባቶችን አላሳፍርም፣ አላሳዝንም እናንተ እዘኑ እንጂ» በማለት ነበር እንደ እናት የሚያዩትንና እንደ ልጅ የሚያየውን ጦሩን ጥሎ በምህረት የገባው፡፡
    ኪዳነና ጓደኞቹ በተጠቀሰው ቀን በሙሉ ምህረት በዘሪማ ከተማ ቢገቡም፣ ሕዝብ በተሰበሰበበት ቦታ በመገኘት «በግል ያጠፋሁት ጥፋት ካለና የገደልኩት ካለ በሽማግሌ አማካኝነት የተፈረደብኝን እከፍላለሁ» በማለት ቃል ገብቷል፡፡ ሌሎችም በተመሳሳይ ሁኔታ ቃል እንደገቡ ይታወሳል፡፡ ነገር ግን በክልሉ ከሕወሓት ጋርና በኋላም ከኢህአዴግ በመወገናቸው ሲዋጓቸው የነበሩና የቤተሰቦቻቸውን ሐብት ንብረት ያወደሙና የነጠቁ ታጣቂዎች በአሁን ወቅት በስልጣን ላይ በመሆናቸው በኪዳነ ጓደኛ ላይ የማቁሰል አደጋ በማድረስና በማሰር ከፍተኛ በደልን በመፈፀም ላይ እንደሚገኙ ሲረዳ ሐዘን ገብቶት እንደነበርና «እኔን አምነው እንዲህ ተሰቃዩ» በማለት ይቆጭ እንደነበርና እርሱም ሆነ ሌሎች ጓደኞቹ የወቅቱን ፖለቲካ ሲየጤኑትና ነገሮችን ሲመለከቷቸው የከተማው ኑሮ አልዋጥ ብሏቸው እንደነበር የቅርብ ወዳጆቹ ይናገራሉ፡፡
    ኪዳነ ማርያም ከቤቱ በር ላይ ሲገደል በቅርብ የነበሩት መጠጥ በመሸጥ የሚተዳደሩት ወ/ሮ እንባ እየተናነቃቸው «ከእርሱ ጋር ሙሉ ምህረት ተደርጐለት በገባው ጉዋደኛው መታሰር ያበሳጨው ስለነበር ወዲያ ወዲህ ብሎ ነገሮችን ካስተካከለ በኋላ ሐሙስ ግንቦት 5 ቀን ጠዋት ጀምሮ ከሳሾቹንና ሽማግሌዎችን በመያዝ እስከ ሰባት ሰዓት እርቅ ሲያደርግ ውሎ በመጨረሻ ተሳካለት፡፡
    ያን ቀን እቤት ሲገባ ደስተኛ ነበር፡፡ ምሳ በልቶ ወደ አድርቃይ ጉዋደኛውን ለማስፈታት እንደሚሄድ ነግሮኝ ከቤት ወጣ አሉ እንባቸውን አብሰው የዚያን ግዜውን ድርጊት አስታወሱና ቀጠሉ
    «ከዚያም ዘጠኝ ሰዓት ከአብሮ አደግ ጓደኞቹ ከሐገሩ ሰዎችና ከአድርቃይ ምክር ቤት አባል ጋር ተመልሶ መጣ፡፡ ምነው ብዬ ብጠይቀው አንድ የሚያስጨርሰው ጉዳይ ስላለ ጉዞውን መሰረዙን ከነገረኝ በኋላ በጣም ሙቀት ስለነበር ሁሉም እበር ላይ ተቀምጠው ጠላ በማስመጣትና በመጠጣት ሲጫወቱ አመሹ፡፡ ኪዳነ አይጠጣም፣ ብቻ በእርቁ መደሰቱን ለመጣው ሁሉ ይናገራል፡፡ ሁለት ሰዓት ሲል ወደ ቤት ውስጥ ገቡ ትንሽ እንደቆዩም እራት አቅርቤላቸው በሉ፡፡ አብዛኛዎቹ ስለሄዱ የቀሩ&#