<?xml version="1.0" encoding="UTF-8"?>
<?xml-stylesheet type="text/css" href="http://www.ectv.org/geezmahtem.css" version="1.0"?>
<rss  version="2.0">
    <channel>
        <title>Amharic News, Ethiopian News, ECTV Zena</title>
        <description>Ethiopian Amharic News, ECTV Zena</description>
        <link>http://www.ectv.org</link>
        <copyright>Copyright ECTV</copyright>
        <docs>http://blogs.law.harvard.edu/tech/rss</docs>
        <lastBuildDate>Tue, 01 Jul 2008 04:28:37 -0400</lastBuildDate>
        <managingEditor>webmaster@ectv.org</managingEditor>
        <pubDate>Tue, 01 Jul 2008 04:27:53 -0400</pubDate>
        <webMaster>webmaster@ectv.org</webMaster>
        <generator>FeedForAll Mac v2.1 (2.1.0.1); http://www.FeedForAll.com/</generator>
        <image>
            <url>http://www.ena.gov.et/AmharicNews/2006/Dec/23Dec06/SImages/12146.jpg</url>
            <title>Amharic News, Ethiopian Zena</title>
            <link>http://www.amhariczena.com</link>
            <description>Ethiopian News</description>
            <width>144</width>
            <height>109</height>
        </image>
        <item>
            <title>በማጭበርበር 50ሺ ብር ሰርቀዋል ተብለው የተጠረጠሩ ሁለት የፌዴራል ኦዲተር ባለሙያዎች ተያዙ</title>
            <description>አዳማ ሰኔ 22/2000/ዋኢማ/ በምሥራቅ ሸዋ ዞን ግንብቹ ወረዳ በቆጠራ ስራ ላይ ተሰማርተው እያሉ 50ሺ ብር ዘርፈው ሊሰወሩ ሞክረዋል ያላቸውን ሁለት የፌዴራል ኦዲተር ባለሙያዎች መያዙን የዞኑ ፖሊስ መምሪያ አስታወቀ።&lt;br /&gt;
 &lt;br /&gt;
በዞኑ ፖሊስ መምሪያ የሕዝብ ግንኙነት ክፍል ሀላፊ ኢንስፔክተር አስቻለው ዓለሙ ለዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል እንዳስታወቁት፤ ተጠርጣሪዎቹ ባለፈው አርብ ሊያዙ የቻሉት የፌዴራሉ ዋና ኦዲተር ባለሙያዎች ነን በማለት የሒሳብ ምርመራ በማድረግ ላይ እንዳሉ ነው።&lt;br /&gt;
 &lt;br /&gt;
የግንብቹ ወረዳ የገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ጽህፈት ቤት ወጪ ያደረገባቸውን ሰነዶች ለመመርመር የተሰማሩ እነዚሁ ሁለት ተጠርጣሪዎች ለሰራተኞች ደመወዝ ተብሎ ከባንክ የወጣውን 700ሺ ብር በመቁጠር ላይ እንዳሉ 50ሺውን ብር በጫማቸው ውስጥ ደብቀው በተከራይዋት የኮንትራት መኪና ለማምለጥ ሞክረው እንደነበር ገልጸዋል።&lt;br /&gt;
 &lt;br /&gt;
ሆኖም ፖሊስ በደረሰው ጥቆማ መሰረት ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር ያዋለ ሲሆን፤ በወቅቱ ባካሄደው ፍተሻ 30ሺ ብር ከአንዱ ተጠርጣሪ የእግር ጫማ ሶል ውስጥ ቀሪው 20ሺ ብር ደግሞ ከሁለተኛው ግለሰብ ኪስ መገኘቱን ተናግረዋል።&lt;br /&gt;
 &lt;br /&gt;
ተጠርጣሪዎቹ በአሁኑ ጊዜ ጉዳያቸው ተጣርቶ ክሱ ለምሥራቅ ሸዋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት መቅረቡን ገልጸው የዓመቱ ሂሳብ በሚዘጋበት በሰኔ ወር ውስጥ እንደዚህ አይነት ድርጊቶች ሊከሰቱ እንደሚችሉ በመገንዘብ የሚመለከታቸው የመንግስት መሥሪያ ቤቶች ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ኢንስፔክተር አስቻለው አሳስበዋል።&lt;br /&gt;
 &lt;br /&gt;
የምሥራቅ ሸዋ ዞን ፖሊስ መምሪያ ሀላፊ ኮማንደር ረቡማ በቀለ በበኩላቸው፤ በሰጡት አስተያየት ተጠርጣሪዎቹ ከፌዴራል ዋና ኦዲተር መሥሪያ ቤት የተጻፈላቸውን ደብዳቤ የያዙ ቢሆኑም ደብዳቤው ሕጋዊ መሆኑንና አለመሆኑን ለማረጋገጥ በአሁኑ ወቅት በማጣራት ላይ እንደሚገኙ ተናግረዋል።</description>
            <link>http://www.waltainfo.com/index.php?option=com_content&amp;task=view&amp;id=947&amp;Itemid=44</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">75D2CE16-4747-11DD-AC17-000393197FB0-2415-000000257E675C70-FFA</guid>
            <pubDate>Tue, 01 Jul 2008 04:28:12 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>የአምቦ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ አዳዲስ የቅድመና ድህረ ምረቃ ትምህርት ፕሮግራሞችን ይጀምራል</title>
            <description><![CDATA[አዲስ አበባ ሰኔ 23/2000/ዋኢማ/ <FONT color="#FF3300">የአምቦ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ በቀጣዩ የትምህርት ዘመን 10 አዳዲስ የቅድመና ድህረ ምረቃ ትምህርት ፕሮግራሞችን ለመጀመር ዝግጅት ማጠናቀቁን አስታወቀ። ሰላሳ ሁለት የምርምር ስራዎችም እየተከናወኑ መሆኑ ተጠቁሟል።</FONT><BR>
 <BR>
የዩኒቨርሲቲ ኮሌጁ ምክትል ዲን አቶ ላቀው ወንድሙ ለዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል እንዳስታወቁት፤ ከሚጀመሩት አዳዲስ የትምህርት ፕሮግራሞች ውስጥ ስድስቱ የቅድመ ምረቃ፣ አራቱ ደግሞ የድህረ ምረቃ ፕሮግራሞች ናቸው።<BR>
 <BR>
የቅድመ ምረቃ ፕሮግራሞቹ ባዮ ፕሮሰሲንግ ኢንጅነሪንግ፣ ቬተርናሪ ላብ ቴክኒዎሎጂ፣ ኢኮኖሚክስ፣ ዳሪሳይንስና የኦሮምኛ ቋንቋ መሆናቸውን የገለጹት አቶ ላቀው፤ በድህረ ምረቃ ደግሞ ኮኦፕሬቲቭ አካውንቲንግ፣ አናለቲካል ኬሚስትሪ፣ ኢንቫይሮመንታል ሳይንስና ፕላንት ፓቶሎጂ እንደሆኑ አመልክተዋል።<BR>
 <BR>
በሚቀጥለው የትምህርት ዘመን በአዳዲሶቹ ፕሮግራሞች 520 ተማሪዎችን ተቀብሎ ማስተማር እንደሚጀምር ጠቁመው፤ ፕሮግራሞቹ የአገሪቱን የሰለጠነ የሰው ኃይል ፍላጎት መሰረት በማድረግ የተዘጋጁ መሆናቸውን ተናግረዋል።<BR>
 <BR>
ኮሌጁ ቀደም ሲል የትምህርት መርጃ መሳሪያዎችን ያዘጋጀና መምህራንንም በቅጥር እያሟላ መሆኑን አመልክተው፤ ከአካባቢው የግብርና ምርምር ተቋማት ጋር በመተባበር ስልጠናውን የተሳካ ለማድረግ መታቀዱን ጠቁመዋል።<BR>
 <BR>
በዩኒቨርሲቲ ኮሌጁ መምህራን 32 የምርምር ተግባራት በመከናወን ላይ ናቸው ያሉት ምክትል ዲኑ፤ ምርምሮቹም በእፅዋት ሳይንስ፣ በእንስሳት፣በባዮሎጂ፣ በኬሚስትሪና በማህበራዊ ሳይንስ ላይ ያተኮሩ መሆናቸውን ተናግረዋል።<BR>
 <BR>
ምርምሩ ከአካባቢው አርሶ አደሮች ጋር በመተባበር የሚካሄዱና ችግሮቻቸውን ለመፍታት በሚያስችል መልኩ እንደሚካሄዱ ጠቁመው፤ ዘንድሮ በ40 በመቶ ክፍያ 20 የውጭ ዝርያ ያላቸው የተጠቁ ጊደሮች መከፋፈላቸውን ገልጸዋል።<BR>
 <BR>
ለምርምሩ ከመንግስትና ከዩኒቨርሲቲ ኮሌጁ የውስጥ ገቢ የተመደበ 155 ሺ ብር ስራ ላይ መዋሉንም ዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል ዘግቧል::]]></description>
            <link>http://www.waltainfo.com/index.php?option=com_content&amp;task=view&amp;id=948&amp;Itemid=44</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">C20243A9-4746-11DD-AC17-000393197FB0-2415-000000232922F01C-FFA</guid>
            <pubDate>Tue, 01 Jul 2008 04:26:53 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>የኢትዮጵያ ማር ወደ አውሮፓ ገበያ ሊገባ ነው</title>
            <description><![CDATA[የኢትዮጵያ ማር ወደ አውሮፓ ገበያ ሊገባ ነው <br />
<br />
በዳዊት ታዬ<br />
<br />
ኢትዮጵያ የማር ምርትን ወደ አውሮፓ ገበያ ለማስገባት የሚያስችላትን ፍቃድ ማግኘትዋንና በተያዘው የፈረንጆች ዓመት ከ6 ሚሊዮን ብር በላይ የሚሆን ማር እንደምትልክ ይጠበቃል፡፡ <br />
<br />
ኢትዮጵያ ማርን ወደ አውሮፓ ገበያ ለማስገባት ሰርተፍኬት ማግኘቷን በተመለከተና በዚህ አዲስ ገበያ መገኘት ዙሪያ ከትናንት በስቲያ በኢምፔሪያል ሆቴል በተደረገ ውይይት ላይ እንደተገለፀው፣ የኢትዮጵያ ማር ወደ አውሮፓ ገበያ እንዲገባ መፈቀዱ ለሌሎች ተመሳሳይ ምርቶች ወደገበያ እንዲገቡ መንገድ ይከፍታል ተብሎ ታምኖበታል፡፡ <br />
<br />
በአሁኑ ጊዜ በኢትዮጵያ ማር አምራቾችና ላኪዎች ማህበር ሥር 15 የሚደርሱ ኩባንያዎች የታቀፉ ሲሆን 6 የሚሆኑት ኩባንያዎች ወደ አውሮፓ ገበያ ሊገባ የሚችለውን የማር ምርት የጥራት ደረጃ የሚያሟሉ በመሆናቸው የማር ምርቶቻቸውን መላክ እንደሚችሉ ተጠቁሟል፡፡ <br />
<br />
ከተያዘው የፈረንጆች አመት ማጠቃለያ ድረስም 300 ቶን ማር ለገበያ ለማቅረብ ፍቃዱን ያገኙ ኩባንያዎች ዝግጅት ማድረጋቸውን የኢትዮጵያ የማር አምራቾችና ላኪዎች ማኅበር ፕሬዚዳንት አቶ ኃይለጊዮርጊስ ደምሴ አስታውቀዋል፡፡ <br />
<br />
በአገሪቱ የማር ምርት ላይ ጥናት ካደረጉትና በውይይቱ ወቅት ማብራሪያ ከሰጡት ባለሙያዎች መካከል አንዱ ዶ/ር ግርማ ሞገስ ወደ አውሮፓ ገበያ ማር ለመላክ ፍቃዱን ያገኙት ስድስቱ ኩባንያዎችና የማህበሩ አባላት ወደ አወሮፓ የሚልኩትን የማር መጠን በሚቀጥለው ዓመት ወደ 1200 ቶን ለማሳደግ እቅድ መያዙንም አመልክተዋል፡፡ <br />
<br />
ይህ ለአገሪቱ የውጭ ምንዛሪ የሚገኝባቸው ምርቶች ብዛትን ከፍ ያደርጋል የተባለው የማር ምርት ተፈላጊነት ያለው በመሆኑ በአሁኑ ጊዜ የአውሮፓ አገሮች አንዱን ቶን በሁለት ሺህ ዶላር የሚገዙ መሆኑን ተጠቅሷል፡፡ <br />
<br />
በዚህ የዋጋ ተመን ዘንድሮ ይላካል ከሚባለው 300 ቶን ማር ከ6 ሚሊዮን ብር በላይ የውጭ ምንዛሪ ይገኛል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ ከዚህ ቀደም ማር ለመላክ ከአውሮፓ ኅብረት ማረጋገጫ ማግኘት ባለመቻሉ ሳይላክ መቆየቱንና አሁን የሚላከውም ለመጀመሪያ ጊዜ ነው፡፡  <br />
<br />
ዶ/ር ግርማ እንዳሉት፣ በአገር ውስጥ ያለው የማር አቅርቦት በአውሮፓ ገበያ ከሚፈለገው መጠን ጋር ሲነፃፀር እጅግ በጣም ዝቅተኛ ነው፡፡ ማር ለማግኘት ገጠር ድረስ መውረድ ያስፈልጋል፡፡ አንድ ኪሎ ማር በገጠር አካባቢ አስራ ስድስት ብር ይገዛል፡፡ ይህ ማር ፕሮሰስ ተደርጎ ለውጭ ገበያ ሊመጥን በሚችል ደረጃ ተዘጋጅቶ እስኪቀርብ ድረስ ከ20 ብር በላይ ሊጠይቅ ስለሚችል የማር ላኪ ኩባንያዎች ከገበሬው የሚሰበስቡትን ማር ብቻ ከመጠበቅ በተጨማሪ ራሳቸው ኩባንያዎቹ ማር በማምረት ሥራ መሰማራት እንደሚኖርባቸው አሳስበዋል፡፡ <br />
<br />
የኢትዮጵያ ማር ትልቁ አሁን በባህላዊ ደረጃ የሚመረተው ማር የጥራት ደረጃ ዝቅተኛ መሆን ነው፡፡ ይህንን ምርት በጥራት አምርቶ ለገበያ ለማቅረብና ወደ አውሮፓ ገበያ ለመግባት የተገኘውን እድል በአግባቡ ለመጠቀም ማር በማምረት ሥራ ላይ ያሉ ብቻ ሳይሆኑ መንግሥትም ጭምር ተሳታፊ መሆን እንዳለበትና ይህ የተሰጠው የገበያ እድል በየአንድ ዓመቱ የሚታደስ በመሆኑ ጥንቃቄ የሚባው መሆኑን የማኅበሩ ፕሬዚዳንት አቶ ኃይለጊዮርጊስ አመልክተዋል፡፡ <br />
<br />
በዚህ ዘርፍ ውስጥ ከምርት ጥራት ባሻገር ዋና ዋና ችግር ናቸው ተብለው የተጠቆሙት የምርት መጠንና የፋይናንስ ችግር ናቸው፡፡ ገበሬው የበለጠ እንዲያመርት በዘመናዊ ቀፎዎች እንዲጠቀም ማድረግ ያስፈልጋል፡፡ ይህንንም ለማድረግ የፋይናንስ ድጋፍ ሊሰጠው ይገባል፡፡ <br />
<br />
የአውሮፓ ህብረት ገበያ ማግኘት ትልቅ ነገር ነው፡፡ የህብረቱ ህግ እጅግ ጠንካራ በመሆኑ ይህንን ሰብሮ መግባት በራሱ ትልቅ ግብ ቢሆንም የምርት ጥራትና የፋይናንስ ድጋፍ ካልታከለበት እድሉ ሊያመልጥ እንደሚቻል መገንዘብ አስፈላጊ መሆኑን ሃይለጊዮርጊስ ይጠቁማሉ፡፡ <br />
<br />
በውይይቱ ወቅት የተገኙት የአዲስ አበባ ንግድና ዘርፍ ማኅበራት ፕሬዚዳንት አቶ እየሱስወርቅ ዛፉ ከአውሮፓ ህብረት የተገኘው ማረጋገጫ በጣም ጠቃሚና በክፍለ ኢኮኖሚው ለሚሳተፉ መልካም የሥራ እድል እንደሚፈጥር አስረድተዋል፡፡ <br />
<br />
ከአውሮፓ ህብረት ማረጋገጫ ያገኘው የማር ገበያ እድል በተጨማሪ ለአውሮፓ ገበያ ሥጋ አይብ ዓሳና የመሳሰሉትን ለማካተት መስራት እንደሚያስፈልግም አሳስበዋል፡፡   <br />
<br />
የማር ምርትን ለአውሮፓ ገበያ ለማቅረብ የኔዘርላንድ መንግሥት ከፍተኛ ድጋፍ በማድረግና በአሁኑ ወቅትም ከማር ላኪዎችና አምራቾች በጀት በመመደብ በመስራት ላይ ይገኛል፡፡ ]]></description>
            <link>http://www.ethiopianreporter.com/content/view/2096/54/</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">00FCC9B1-420B-11DD-BF88-000393197FB0-14351-000000F77CF6A2BB-FFA</guid>
            <pubDate>Tue, 24 Jun 2008 12:35:07 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>አየር መንገድ ቻይናውያን የአውሮኘላን አስተናጋጆችን ሊቀጥር ነው</title>
            <description><![CDATA[አየር መንገድ ቻይናውያን የአውሮኘላን አስተናጋጆችን ሊቀጥር ነው<br />
<br />
በዳዊት ታዬ<br />
<br />
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአውሮኘላን ውስጥ የመስተንግዶ አገልግሎት የሚሰጡ (ሆስተሶች) ቻይናውያንን ቀጥሮ ሊያሰራ ነው፡፡<br />
ከአየር መንገዱ ያገኘነው መረጃ እንደሚያስረዳው አየር መንገዱ በሆስተስነት ቀጥሮ ለማሰራት ባወጣው እቅድ መሠረት አምስት የሚሆኑ ቻይናውያንን በመምረጥ በበረራ መስተንግዶ ማእከሉ ውስጥ በማሰልጠን ላይ ይገኛል፡፡<br />
<br />
ከአየር መንገዱ የህዝብ ግንኙነት የተገኘው ይኸው መረጃ ጨምሮ እንደሚያስረዳው ቻይናውያን ሆስተሶችን ለመቅጠር የተፈለገው ወደ ቻይና የሚደረጉ በረራዎች በመጨመራቸውና በዚህም በረራ የቻይና ዜጐች በመበራከታቸው ነው፡፡ <br />
<br />
በአሁኑ ወቅት የኢትዮጵያ አየር መንገዱ በሳምንት ወደ ቤጂንግ አምስት ጊዜ፣ ወደ ጓንዥ አምስት ጊዜ፣ ወደ ሆንግ ኮንግ ደግሞ ሦስት ጊዜ በመብረር ላይ ይገኛል፡፡ ከመጪው ወር ጀምሮ ደግሞ ተጨማሪ በረራዎች የሚጨምር በመሆኑና አሁን ካለው መንገደኞች በላይ የሚጠበቅ በመሆኑ እነዚህን የቻይና ዜጐች በቋንቋቸው ማስተናገድ አስፈልጓል፡፡ ከዚህም ሌላ በኢትዮጵያና በቻይና መንግሥታት መካከል ያለው ግንኙነት እየተጠናከረ በመምጣቱም ለአየር መንገድ እርምጃ አስተዋፆኦ አድርጓል፡፡ <br />
<br />
የቻይና ዜጐች በአብዛኛው በራሳቸው ቋንቋ የሚጠቀሙና ኢትዮጵያውያን ሆስተሶች በዚህ ቋንቋ መጠቀም ስለማይችሉ እነዚህን ቻይናውያን ደንበኞች በራሳቸው ቋንቋ የተቀላጠፈ አገልግሎት እንዲያገኙ በማሰብ የተወሰደ እርምጃ ሲሆን ቻይናዎቹ ሆስተሶች የሚመደቡትም ወደ ቻይና በሚደረጉ የአየር መንገዱ የበረራ መስመሮች ላይ ብቻ እንደሆነም ተጠቁሟል፡፡ <br />
<br />
አየር መንገዱ ድርጅቱን ሲቋቋም አካባቢ ኢትዮጵያውያን ሆስተሶችን ለማግኘት አስቸጋሪ ስለሆነበት የውጭ ሆስተሶችን ቀጥሮ ያሰራ የነበረ ሲሆን ኢትዮጵያውያን በዚህ ሥራ መሰማራት ከጀመሩ ወዲህ ግን የውጭ ሆስተሶችን መቅጠር አቁሞ ሙሉ በሙሉ ኢትዮጵያውያን ሆስተሶች አገልግሎት በመስጠት ላይ እንደሚገኙ ይታወቃል፡፡ <br />
<br />
በአሁኑ ጊዜ የኢትዮጵያ አየር መንገድ 539 የሚሆኑ ሆስተሶች በሥራ ላይ የሚገኙ ሲሆን ሁሉም ኢትዮጵያውያን ናቸው፡፡ 316 የሚሆኑ ሆስተሶች ደግሞ በሥልጠና ላይ ናቸው፡፡ ]]></description>
            <link>http://www.ethiopianreporter.com/content/view/2067/54/</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">DBC3F3D8-420A-11DD-BF88-000393197FB0-14351-000000F70153EBA0-FFA</guid>
            <pubDate>Tue, 24 Jun 2008 12:31:31 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>የኢትዮጵያ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያና የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ፈተና እርማት ተጀመረ</title>
            <description><![CDATA[አዲስ አበባ ሰኔ 17 2000/ዋኢማ/ የኢትዮጵያ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያና የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ፈተና ተጠናቆ እርማት መጀመሩን የአጠቃላይ ትምህርት ጥራት ማረጋገጫና ፈተናዎች ኤጀንሲ አስታወቀ።<br />
የኤጀንሲው ተጠባባቂ ስራ አስኪያጅ አቶ ታከለ ገብረ ኪዳን ለዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል እንዳስታወቁት፤እርማቱ በፍጥነት የተጀመረው ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ለመግባት የመግቢያ ፈተና ለወሰዱ ተማሪዎች በሀምሌ መጀመሪያ፣ የአጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቅያ ፈተና ለወሰዱት ተፈታኞች ደግሞ በነሀሴ ወር ውስጥ ውጤት ለማሳወቅ ታስቦ ነው።<br />
 <br />
 <br />
ፈተናዎቹ በ1ሺ 236 አስፈታኝ ትምህርት ቤቶች እንደተሰጡ ጠቁመው፤ መምህራን በሚያስተምሩባቸው ትምህርት ቤቶች እንዳይፈትኑ መደረጉ ለሰኬታማነቱ አስተዋፅኦ ማበርከቱን ተናግረዋል።<br />
 <br />
 <br />
ፈተናውን 961ሺ 641 የአስረኛ 91ሺ 660 የአስራ ሁለተኛ ክፍል ተፈታኞች እንደወሰዱ አስታውሰው፤ የፈተና እርማቱን ለማቀላጠፍ ስድስት ፈጣን ማረሚያ ማሸኖች መገዛታቸውንና የኤጀንሲው ሰራተኞች ከቴክኒክና ሙያ ዲፕሎማ ተመራቂ ተማሪዎች ጋር በመሆን እየሰሩ መሆናቸውን ገልፀዋል።<br />
 <br />
 <br />
በአብዛኛው የዕርማቱን ጊዜ የሚያጓትተው ተማሪዎቹ በመልስ መስጫው ወረቀት ላይ ሲያጠቁሩ የሚፈጥሩትን ስህተት ለማረም የሚደረገው ጥረት መሆኑን ጠቁመው፤ የማረሚያ ማሽኖች ችግር ካላጋጠማቸውና መብራት መቆራረጥ ካለተፈጠረ የከፍተኛ ትምህርት መግቢያውም ሆነ የአስረኛ ክፍል ፈተና ውጤት በታቀደው ጊዜ ሊገለፅ እንደሚችል ተናግረዋል።<br />
 <br />
 <br />
በታቀደው ጊዜ ውስጥ ውጤቱን ለመግለፅ እንዲቻል መብራት ሀይል መብራት እንዳይቋረጥ እያደረገ ያለው ትብብርም ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ አቅርበዋል።<br />
 <br />
 <br />
ከፈተና ጣቢያዎች ጋር የሚደረገው የመልስ መሰጫ ወረቀት ርክክብ እስካሁን ሙሉ ለሙሉ እንዳልተጠናቀቀ ጠቁመው፤ ከርክክቡ ጎን ለጎን የእርማት ስራው እየተከናወነ እንደሆነ መናገራቸውን ዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል ዘግቧል።]]></description>
            <link>http://www.waltainfo.com/index.php?option=com_content&amp;task=view&amp;id=776&amp;Itemid=44</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">DEA4A7AC-4208-11DD-BF88-000393197FB0-14351-000000F0663DC3C4-FFA</guid>
            <pubDate>Tue, 24 Jun 2008 12:23:03 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>የጎንደር ከተማ አቋራጭ መንገድ ግንባታ በ60 ነጥብ 9 ሚሊየን ብር እንደሚካሄድ ተገለፀ</title>
            <description><![CDATA[አዲስ አበባ ሰኔ 17/2000/ዋኢማ/ የጎንደር ከተማ አቋራጭ መንገድ ግንባታ በ60 ነጥብ 9 ሚሊየን ብር ወጪ እንደሚከናወን የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን አስታወቀ። የመንገድ ግንባታውን ለማከናወን የሚያስችል ስምምነት ዛሬ ተፈርሟል።<br />
 <br />
የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ዛይድ ወልደ ገብረኤል በስምምነቱ ላይ እንዳስታወቁት፤ ከመንግስት በተመደበ በጀት የሚገነባው አቋራጭ መንገድ 10 ነጥብ 2 ኪሎ ሜትር ርዝመት አለው።<br />
 <br />
በአስፋልት ኮንክሪት ከሚሰራው ውስጥ አራት ኪሎ ሜትሩ ነባር የጠጠር መንገድ ሲሆን፣ ቀሪው አዲስ መሆኑን ጠቁመው፤ መንገዱ በባለስልጣኑ የራስ ኃይል ኮንስትራክሽን እንደሚሰራና የውስጥ አቅምን በማጠናከር ረገድ አስተዋጽኦ እንዳለው ጠቁመዋል።<br />
 <br />
የመንገድ ግንባታ ስምምነቱን የፈረሙት በባለስልጣኑ የኢንጂነሪንግና ሪጉላቶሪ ዋና መምሪያ ምክትል ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ዘርፉ ተሰማና በኦፕሬሽን ዋና መምሪያ የራስ ኃይል ኮንስትራክሽን ስራ አስኪያጅ አቶ መስፍን ኃይሌ ናቸው።<br />
 <br />
አቶ ዘርፉ ተሰማ በስምምነቱ ስነስርዓት ላይ እንደገለጹት፤ የአቋራጭ መንገዱ መገንባት ከአዲስ አበባ አዘዞ ጎንደር በሚወስደው መንገድ ላይ ያለውን የትራፊክ መጨናነቅ ለማስቀረት ይረዳል።<br />
 <br />
በተጨማሪም መንገዱ በዋናው መንገድ ላይ ያለውን ጉዞ ከማሳጠሩም በላይ አሽከርካሪዎች በምቾት እንዲያሽከረክሩእንደሚያግዛቸው ጠቁመው፤ ግንባታውን በአንድ አመት ጊዜ ውስጥ ለማጠናቀቅ ዕቅድ መያዙን አመልክተዋል።<br />
 <br />
የራስ ኃይል ኮንስትራክሽን ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ መስፍን ኃይሌ በበኩላቸው፤ መንገዱን በተያዘለት ጊዜ በጥራት ሰርተው ለማስረከብ ቃል ገብተዋል።<br />
 <br />
ባለስልጣኑ በተለያዩ ፕሮጀክቶች ከፋፍሎ ሲያካሂድ የነበረው የአዲስ አበባ ጎንደር መንገድን በአስፋልት ኮንክሪት የማልበስ ስራ በመጠናቀቅ ላይ እንደሆነ ባለስልጣኑ መግለጹን ዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል ዘግቧል።]]></description>
            <link>http://www.waltainfo.com/index.php?option=com_content&amp;task=view&amp;id=777&amp;Itemid=44</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">984D3E10-4208-11DD-BF88-000393197FB0-14351-000000EF7C98D675-FFA</guid>
            <pubDate>Tue, 24 Jun 2008 12:16:14 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>ኢትዮጵያ በኢኮኖሚውና በዲፕሎማሲ ዘርፍ ተጨባጭ ውጤቶችን ማስመዝገቧ ተገለፀ</title>
            <description><![CDATA[አዲስ አበባ ሰኔ 17/2000/ዋኢማ/ኢትዮጵያ ኢኮኖሚውን፣ ዲፕሎማሲውንና የቀጠናውን ሰላም ለማረጋገጥ እያደረገች ባለው እንቅስቃሴ ተጨባጭ ውጤት በማስመዝገብ ላይ መሆኗን የውጭ ጉዳይ ሚንስትር አቶ ስዩም መስፍን አስታወቁ።<br />
 <br />
ሚንስትሩ አቶ ስዩም መስፍን ዛሬ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርን የ2000 በጀት ዓመት የአስር ወራት የዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባቀረቡበት ውቅት እንደገለፁት፤ በኢኮኖሚና ዲፕሎማሲ ዘርፍ በተሰራው የመሰረታዊ ስራ ሂደት ለውጥ ጥናት መሰረት የውጭ ኢንቨስተሮችን ለመሳብ የተደረገው እንቅስቃሴ አበረታች ውጤት እያመጣ ነው።<br />
 <br />
ለሀገራችን ወጪ ምርቶች ገዥዎችን ለማፈላለግ እንዲሁም ለልማትና ዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ አጋዥ የሆኑ የልማት፣ ፋይናንስና ቴክኒክ ተራድኦ ለማግኘት በጥናት ላይ የተመሰረተና በተግባር ላይ ያተኮረ ዕቅድ ይዞ እየሰራ መሆኑንም አቶ ስዩም አስረድተዋል።<br />
 <br />
የኤርትራ መንግስት የአገራችንን ሰላም ለማደፍረስና አካባቢውን ቀውስ ውስጥ ለመክተት ለሚፈፀማቸው የሽብር ተግባራት ተጠያቂ እንዲሆንና የድንበርና የካሳ ጉዳይ ክርክሮች የአገሪቱን ጥቅም ባስከበረ መልኩ እንዲከናወኑ መደረጉንም ገልፀዋል።<br />
 <br />
የሶማሊያ የሽግግር መንግስት ዘላቂ ሰላም ለማምጣት የሚያደረገውን ጥረት በመደገፍ በአገሪቱ የተሰማራው የኢትዮጵያ ሰራዊት ተልኮውን አጠናቆ ወደ አገሩ እንዲመለስ ፣ እንዲሁም የሰላም እስከባሪ ኃይል እንዲሰማራ ዲፕሎማሲያዊ ተግባራት መከናወናቸውን ሚንስትሩ አስረድተዋል።<br />
 <br />
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የማስፈፀም አቅምን በመገንባት ተቋማዊ ለውጥ ለማምጣትና በንግድ፣ በቱሪዝም ማስፋፋት፣ በባለሀብት ምልመላ፣ በልማት ፋይናንስ፣ በፕብሊክ ዲፕሎማሲና ህዝብ ግንኙነት እንዲሁም በመልካም ገፅታ ግንባታ የተሻለ አፈፃፀም መከናወኑን ተናግረዋል።<br />
 <br />
የሪፖርቱን መቅረብ ተከትሎ የምክር ቤቱ አባላት በሱማሊያ ጉዳይ ፣ በኤርትራ ተንኳሽ ባህሪና መወሰድ ስላለባቸው ርምጃዎች፣ ከሱዳን ጋር የድንበር ማካለል ሂደትና መሰል ጉዳዮች ላይ ጥያቄዎች ቀርበው ሚኒስትሩ አቶ ስዩም መስፍን ምላሽና ማብራሪያ መስጠታቸውን ዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል ዘግቧል።]]></description>
            <link>http://www.waltainfo.com/index.php?option=com_content&amp;task=view&amp;id=775&amp;Itemid=44</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">747BC2CF-4208-11DD-BF88-000393197FB0-14351-000000EF059FBFBF-FFA</guid>
            <pubDate>Tue, 24 Jun 2008 12:14:16 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>በደቡብ ክልል ዘንድሮ ከ54ነጥብ 9 ሚሊየን በላይ የቡና ችግኞች ለተከላ ተዘጋጁ</title>
            <description><![CDATA[ሐዋሳ ሰኔ 10/2000/ ዋኢማ/በደቡብ ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ክልል ዘንድሮ ከ54ነጥብ 9 ሚሊየን በላይ የቡና ችግኞች ለተከላ መዘጋጀታቸውን የክልሉ ግብርናና ገጠር ልማት ቢሮ አስታወቀ።በበጀት ዓመቱ ከ134ሺ ቶን በላይ የቡና ምርት መገኘቱም ተመልክቷል።<br />
 <br />
የቢሮው የህዝብ ግንኙነት መምሪያ ኃላፊ አቶ ተስፋየ ይገዙ ዛሬ ለዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል እንዳስታወቁት፤ ዘንድሮ በክልሉ ምዕራባዊና ደቡባዊ ዞኖች በመንግስትና በግል የችግኝ ጣቢያዎች 54ሚሊየን 980ሺ 767 ችግኞች ተፈልተው ለተከላ ተዘጋጅተዋል።<br />
 <br />
በበጀት ዓመቱ ለተከላ ከተዘጋጁት ችግኞች መካከልም 46ሚሊየን 903ሺ787 በግል የችግኝ ጣቢያዎች የተዘጋጁ መሆኑን የጠቆሙት መምሪያ ኃላፊው፤ ቀሪው 8ሚሊየን 76ሺ 980 የሚሆኑት ደግሞ በመንግስት የችግኝ ጣቢያዎች መሆናቸውን አስረድተዋል።<br />
 <br />
ችግኞቹን ለማፍላትም በመንግስትና በግል ከ70 ነጥብ 4 ሚሊየን በላይ የቡና ዘር በችግኝ ጣቢያዎቹ የማፍሰስ ስራ መከናወኑን አቶ ተስፋየ አመልክተው፤ ተዘርተው የበቀሉት ከ54 ሚሊየን በላይ ችግኞችም በአሁኑ ወቅት ከአራት እስከ ሰባት ቅጠል ደረጃ መድረሳቸውን አመልክተዋል።<br />
 <br />
ይህ በእንዲህ እንዳለ ዘንድሮ በክልሉ ቡና አብቃይ ዞኖችና ልዩ ወረዳዎች ወደ ስራ በገቡ 399 የታጠበና 128 የደረቅ ቡና ማዘጋጃዎች አማካኝነት 134ሺ 880 ቶን የቡና ምርት ለማግኘት መቻሉን አቶ ተስፋየ አስታውቀዋል።<br />
 <br />
በበጀት ዓመቱ የተገኘው የቡና ምርትም ከዕቅዱ ከ95 በመቶ በላይ መከናወኑን ያመለከቱት መምሪያ ኃላፊው፤ ጥራቱን እንዲጠብቅ የሚያስችሉ ስራዎች በስፋት መተግበራቸውን አመልክተዋል።<br />
 <br />
በዚህም በ189ሺ666 ሄክታር መሬት ላይ የኩትኳቶ ስራ የተከናወነ ሲሆን፤ 42ሺ761 ቶን ኮምፖስትም ተዘጋጅቶ ጥቅም ላይ መዋሉን አስረድተዋል።<br />
 <br />
እንዲሁም 949ሺ 405 ካሬ ሜትር የቡና ማድረቂያ ቆጥ ተሰርቶ ለአገልግሎት እንዲውል መደረጉንም ከአቶ ተስፋየ ገለፃ ለመረዳት መቻሉን ዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል ዘግቧል።]]></description>
            <link>http://www.waltainfo.com/index.php?option=com_content&amp;task=view&amp;id=577&amp;Itemid=44</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">1C82284C-3C8C-11DD-B05D-000393197FB0-5869-0000006069AAE9CB-FFA</guid>
            <pubDate>Tue, 17 Jun 2008 12:42:29 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>አየር መንገዱ በአውሮፕላን አብራሪነት ያሰለጠናቸውን 18 ፓይለቶች አስመረቀ</title>
            <description>አዲስ አበባ ሰኔ 10 /2000/ዋኢማ/የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአውሮፕላን አብራሪነት ትምህርታቸውን የተከታተሉ 18 ፓይለቶችን ዛሬ አስመረቀ።&lt;br /&gt;
በምርቃት ስነ ስርዓቱ ላይ በአየር መንገዱ የበረራ ስልጠና ስራ አስኪያጅ ካፒቴን ለማ ተካልኝ እንደተናገሩት፤ ሰልጣኞቹ ባለፉት ሁለት ዓመታት በኮሜርሻል ፓይለት ላይሰንስ፣ በኢንስትሩመንት ሬቲንግና በመልቲ ጄነሬቲግ ሙያዎች ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የቆዩ ናቸው።&lt;br /&gt;
 &lt;br /&gt;
ከተመራቂ ፓይለቶች መካከል 12 ኢትዮጵያዊያን ሲሆኑ ስድስቱ ፓይለቶች ደግሞ ከቻድ የመጡ መሆናቸውን ገልጸው፤ አየር መንገዱ ባለፉት ዓመስት ዓመታት በከፍተኛ ሁኔታ እያደገ በመምጣቱ ፓይለቶችን በየወቅቱ ማሰልጠንና ወደሙያው ማስገባት ላይ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ነው ብለዋል።&lt;br /&gt;
 &lt;br /&gt;
በመሆኑም በአሁኑ ወቅት ከስድስት ሚሊየን ዶላር በላይ በሆነ ወጪ10 የመለማመጃ አውሮፕላኖችን ለመግዛት የሚያስችል ዝግጅት መጠናቀቁን ካፒቴን ለማ ጠቁመው፤ በአየር መንገዱ ውስጥ በቀጣይም በርካታ ፓይለቶች ስለሚያስፈልጉ የስልጠና ተግባሩ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቀዋል።&lt;br /&gt;
 &lt;br /&gt;
የአየር መንገዱ ኦፕሬሽን ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ተወልደገብረ ማሪያም በበኩላቸው፤ በአሁኑ ወቅት አየር መንገዱ በኤክሰፖርት ዘርፍና በመንገደኛ የሚደረጉ በረራዎችን በአስተማማኝ ማስተናገድ የሚቻልበት ደረጃ ላይ መደረሱን ጠቁመው፤ ከተለያዩ አገራት ጋር የበረራ ግንኙነቶችን በማድረግ በተያዘው ዓመት ከፍተኛ አፈጻጸም ማሳየቱን ተናግረዋል።&lt;br /&gt;
 &lt;br /&gt;
ተመራቂ ተማሪዎች በስነሰርዓቱ ላይ ባስተላለፉት መልክት በሚቀጥለው የስራ ዘመን የሚጠበቅባቸውን ሁሉ በታማኝነትና በቅንነት ለማገልገል ቃል መግባታቸውን ዋልታ ኢንፎርሜን ማዕከል ዘግቧል።</description>
            <link>http://www.waltainfo.com/index.php?option=com_content&amp;task=view&amp;id=583&amp;Itemid=44</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">BD132206-3C8B-11DD-B05D-000393197FB0-5869-0000005F2CAD7DF5-FFA</guid>
            <pubDate>Tue, 17 Jun 2008 12:40:35 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>ኮሚሽኑ የቦንጋና የዲማ ስደተኞች መጠለያ ጣቢያዎች መዘጋታቸውን አስታወቀ</title>
            <description><![CDATA[አዲስ አበባ ሚያዚያ 29/2000/ዋኢማ/ በምዕራብ ኢትዮጵያ የሚገኙትን የቦንጋና ዲማ የስደተኞች መጠለያ ጣቢያዎች በይፋ መዝጋቱን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስደተኞች ኮሚሽን አስታወቀ። በጣቢያዎቹ ተጠልለው የነበሩ 23 ሺ የሱዳን ስደተኞች በኮሚሽኑ ድጋፍ ተጠቃለው ወደ አገራቸው መመለሳቸውን ገልጿል።<br />
<br />
ኮሚሽኑ በድረ ገጹ ይፋ ባደረገው ዘገባ እንዳስታወቀው፤ በምዕራብ ኢትዮጵያ የሚገኙት ሁለቱ የስደተኞች ጣቢያዎች እንዲዘጉ የተደረገው በጣቢያዎቹ ተጠልለው የነበሩ ስደተኞች በደቡባዊ ሱዳን ወደ ሚገኘውና መኖሪያቸው ወደ ነበረው ብሉናይል ክፍለ ሃገር ከተመለሱ በኋላ ነው።<br />
<br />
ከሁለቱ ጣቢያዎች ስደተኞችን ወደ አገራቸው የመመለሱ ስራ ከተጀመረበት እንደ አውሮፓ አቆጣጠር ከግንቦት 2006 ወዲህ 28 ሺ የሚደርሱ ሱዳናውያን ከጣቢያዎቹ ወደ አገራቸው መመለሳቸውን ኮሚሽኑ አመልክቶ ከነዚህ መካከል 2ሺ ያህሉ በራሳቸው መንገድ ወደ ትውልድ ስፍራቸው የተመለሱ መሆናቸውን ገልጿል።<br />
<br />
አሁን በተዘጉ ሁለቱ ጣቢያዎች የቀሩ 3ሺ የሚጠጉ ስደተኞች ጋምቤላ ክልል ወደሚገኘው የፊኝዶ ጣቢያ ወይም በቤንሻንጉል ጉሙዝ ወደሚገኘው የሸርቆሌ መጠሊያ ጣቢያ እንደሚተላለፉ ኮሚሽኑ አስታውቋል።<br />
<br />
ኮሚሽኑ ከኢትዮጵያ መንግስትና ከሌሎች አጋሮቹ ጋር በመሆን በኢትዮጵያ በሚገኘው ቡድኑ አማካኝነት የስደተኞች መጠለያ የነበሩት ካምፖችና መሰረተ ልማቶች ለአካባቢው ማህበረሰብ ግልጋሎት ሊሰጡ በሚችሉበት ሁኔታ ላይ እየሰራ መሆኑን አመልክቷል።<br />
<br />
በጣቢያዎቹ ውስጥ የሚገኙ የውሃ ተቋማት፣ ትምህርት ቤቶች፣ የጤና ተቋማት፣ ቢሮዎች፣ የሙያ ማሰልጠኛዎችና የመኖሪያ አካባቢዎችን ከነቁሳቁሳቸው ለነዋሪዎች የማስረከብ ስራ እንደሚሰራም ኮሚሽኑ ጠቁሟል።<br />
<br />
የመንግስታቱ ድርጅት የስደተኞች ኮሚሽን ከ30 ሺ የሚበልጡ የሱዳን ስደተኞች በፈቃደኝነት ከኢትዮጵያ ወደ አገራቸው እንዲመለሱ መርዳቱን ድረ ገጹ አመልክቷል።<br />
<br />
ከኢትዮጵያ፣ ኡጋንዳ፣ መካከለኛው አፍሪካ፣ ኮንጎ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክና ኬኒያ ወደ አገራቸው ከተመለሱት 275ሺ የሱዳን ስደተኞች መካከል 125ሺ ያህሉ በኮሚሽኑ ድጋፍ የተመለሱ መሆናቸውን ማመልከቱን ዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል ዘግቧል።]]></description>
            <link>http://www.waltainfo.com/AmNews/2008/May/07May08/46548.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">4D6669F1-1D17-11DD-BF19-000393197FB0-6660-00000083A9A9CF9A-FFA</guid>
            <pubDate>Thu, 08 May 2008 11:58:09 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>ካሪቡ ቡና የኢትዮጵያን ቡና በሰሜን አሜሪካ ለማከፋፈል ፍቃድ እንደተሰጠው ተገለጸ</title>
            <description>አዲስ አበባ ሚያዚያ 29/2000/ ከተለያዩ አገራት ቡናን በመግዛትና በማሰራጨት በሰሜን አሜሪካ በትልቅነቱ ሁለተኛ ደረጃ የያዘው ካሪቡ ቡና የቡና አምራቾችን ተጠቃሚ ባደረገ መልኩ የኢትዮጵያን ቡና ለማሰራጨት መስማማቱን አስታወቀ።&lt;br /&gt;
&lt;br /&gt;
ሲ ኤስ አር ዋዬር የተባለ የዜና ድረ ገጽን ጠቅሶ ዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል እንደዘገበው፤ ካሪቡ ቡና የኢትዮጵያ የቡና ምርቶች ለማሰራጨት የሚያስችለውን ፍቃድ አግኝቷል።&lt;br /&gt;
&lt;br /&gt;
ካሪቡ ቡና ባገኘው ፍቃድ መሰረት የቡና አምራቾችን ተጠቃሚ ባደረገ መልኩ የኢትዮጵያን የቡና ምርቶች እንደሚያከፋፍል ዘገባው አመልክቷል።&lt;br /&gt;
&lt;br /&gt;
ካሪቡ ቡና ከኢትዮጵያ ጋር ስምምነት ከፈጸመ በኃላ የደርጅቱ የስራ ሀላፊ ሚስተር ፓወል ቱሬክ እንደተናገሩት ፤ ድርጅቱ ባገኘው ፍቃድ ለሸማቾች የኢትዮጵያን ቡና ጥራት በማስተዋወቅ የቡና አምራቾችን ሕይወት የመለወጥ ስራ ይሰራል።&lt;br /&gt;
&lt;br /&gt;
የኢትዮጵያ አእምሮኣዊ ንብረት ጽህፈት ቤት ዋና ዳይሬክተር አቶ ጌታቸው መንግስቱ በበኩላቸው የኢትዮጵያ መንግስት የኢትዮጵያ የቡና አምራቾችን ጥቅም ማስጠበቅን ቅድሚያ በመስጠት በመስራት ላይ መሆኑን ጠቁመው፤ ስምምነቱ የዚሁ አካል መሆኑን መግለጻቸውን ሲ ኤስ አር ዋዬር የተባለ የዜና ድረ ገጽን ጠቅሶ ዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከልዘግቧል።</description>
            <link>http://www.waltainfo.com/AmNews/2008/May/07May08/46540.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">26D3A808-1D17-11DD-BF19-000393197FB0-6660-00000083298A153D-FFA</guid>
            <pubDate>Thu, 08 May 2008 11:56:20 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>በኤርትራ ያለው አምባገነን ስርዓት ህዝቡ እምነቱን በነጻነት እንዳያራምድ የሚያደርገው ጫና መጠናከሩ ተገለጸ</title>
            <description><![CDATA[አዲስ አበባ ሚያዚያ 28/2000/ዋኢማ/ የኢሳያስ መንግስት ኤርትራውያን በአገራቸው ዕምነታቸውን በነጻነት እንዳያራምዱ እንደሚከለክልና የሃይማኖት ነጻነትን እንደማያከብር ሁለት የሃይማኖት አባቶች አስታወቁ። ኤርትራውያን በተባበረ ትግል ጨቋኙን አገዛዝ እንዲያስወግዱም ጥሪ አቅርበዋል።<br />
<br />
የሃይማኖት አባቶቹ ለዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል እንዳስታወቁት፤ በኤርትራ የሁሉም ዕምነት ተከታዮች ዕምነታቸውን በነጻነት ማራመድ የሚችሉበት ሁኔታ የለም።<br />
<br />
የኤርትራ ካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የሃይማኖት አባት የሆኑትና በለንደን በስደት ላይ የሚገኙት አባ ኃይለማሪያም ዘርዓዮሃንስ እንደገለጹት፤ የኢሳያስ አምባገነን አገዛዝ በአገሪቱ ሙስሊሞች ላይ በቀጥታ ከሃይማኖቱ ጋር የተያያዙ ድርጊቶችን ለምን ፈጸማችሁ በማለት የዕምነቱን መሪዎችና ተከታዮች በማሳደድና በማሰቃየት የጀመረውን ፀረ እምነት እንቅስቃሴ በሌሎች እምነቶችም ላይ ቀጥሎበታል።<br />
<br />
ተሳታፊዎች<br />
በኤርትራ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን አማኞችም ላይ እያደረሰ ያለው በደል በእምነቱ የማይፈቀደውን ፓትርያርክን አውርዶ አዲስ እስከመሾም የሚደርስ መሆኑን ገልጸው በወንጌላውያንና በካቶሊክ ዕምነት ተከታዮችም ላይ በደል ማድረሱን እንደገፋበት አመልክተዋል።<br />
<br />
ኤርትራውያን የሃይማኖት መሪዎችና ተከታዮች አንዱ ሲነካ ሌሎቹ በጋራ ባለመቃወማቸው አምባገነኑ መንግስት ለሚከተለው ነጣጥሎ የማጥቃት ፖሊሲ መጋለጣቸውንና የጥቃቱ ሰለባ መሆናቸውን አመልክተው፤ ህዝቡና የኤርትራ ተቃዋሚ ኃይሎች በተባበረ ክንድ አምባገነኑን ስርዓት መጣልና በምትኩ ዴሞክራሲያዊ ስርዓት መገንባት እንደሚገባቸው አሳስበዋል።<br />
<br />
የኤርትራ ሙስሊም ማህበረሰብ የሃይማኖት መሪ የሆኑት መሃሙድ መሃመድ ኡስማን አልአሚን በበኩላቸው፤ መንግስቱ በሁሉም እምነቶች መሪዎችና ተከታዮች ላይ የሚያደርሰው በደል ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተባባሰ መምጣቱን ገልጸዋል።<br />
<br />
ህዝቡን በማሰር፣ በግዳጅ ወደ ወታደራዊ ማሰልጠኛ በመላክና የዕምነት ቦታዎችን ባለማክበርና የሃይማኖት መሪዎችን በማሰር እምነትን በነጻ የማራመድ መብትን እንደሚጥስ ገልጸው፤ ህዝቡና የአምባገነኑ ስርዓት ተቃዋሚዎች በጋራ የሚያካሂዱትን ትግል ማፋፋምና ነጻነታቸውን ማስከበር ይገባቸዋል ብለዋል።<br />
<br />
ዓለም አቀፉ ማህበረሰብና ጎረቤት አገሮችም በስርዓቱ በሚደርስባቸው ግፍና በደል ከአገራቸው ለሚሰደዱ ዜጎች እያደረጉ ያሉትን ድጋፍ ስርዓቱን ለመጣል የሚደረገውን ትግል በማገዝ ለኤርትራውያን እፎይታ እንዲሰሩ ጥሪ ማቅረባቸውን ዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል ዘግቧል።]]></description>
            <link>http://www.waltainfo.com/AmNews/2008/May/06May08/46519.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">F5BAE82F-1D16-11DD-BF19-000393197FB0-6660-00000082867611F5-FFA</guid>
            <pubDate>Thu, 08 May 2008 11:55:16 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>የኤርትራና የጅቡቲ የድንበር ፍጥጫ ወደ ግጭት እንዳያመራ ተመድ ጠልቃ እንዲገባ ጂቡቲ ጥሪ አቀረበች</title>
            <description><![CDATA[አዲስ አበባ ሚያዚያ 29/2000/ዋኢማ/ ኤርትራ የጂቡቲን ድንበር ጥሳ በመግባቷ የተፈጠረውን የሁለቱ ሀገራት የድንበር ላይ ፍጥጫ ወደ ግጭት እንዳያመራ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጣልቃ እንዲገባ ጂቡቲ ጠየቀች።<br />
<br />
ኤ ኤፍ ፒን ጠቅሶ ዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል እንደዘገበው፤ ኤርትራ የጂቡቲን ድንበር ጥሳ መግባቷን ጅቡቲ ማስታወቋን ገልጾ ፍጥጫው ወደ ጦርነት እንዳያመራ የፀጥታው ምክር ቤት አስፈላጊውን እርምጃ እንዲወስድ ጥሪ አቅርባለች።<br />
<br />
የጂቡቲ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሚስተር መሐመድ አሊ ዩሱፍ ለዜና ምንጩ እንደተናገሩት፤ ኤርትራ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በሁለቱ ሀገራት ድንበር ላይ ጦሯን በማከማቸት ላይ ብትሆንም ሀገራቸው የጦርነት ውጥረቱን በአፍሪካ ህብረትና በአረብ ሊግ አማካይነት በዲፕሎማሲያዊ መንገድ ለመፍታት ቅድሚያ ሰጥታለች ብለዋል።<br />
<br />
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ለወቅቱ የፀጥታው ምክር ቤት ሊቀመንበር ለሆኑትና በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የእንግሊዝ አምባሳደር ጆን ሳዌርስ በፃፉት ደብዳቤ ፤ ኤርትራ ጦሯን ከጅቡቲ ድንበር እንድታስወጣ ያደረገችው ጥረት ውጤት አልባ መሆኑን አመልክተዋል።<br />
<br />
በአሁኑ ጊዜ የሁለቱ አገራት ጦር ራስ ዱመራ በተባለ የድንበር ላይ ተራራ ተፋጠው የሚገኙ ሲሆን፤ ቦታው በቀይ ባህር የሚንቀሳቀሱትን መርከቦች በርቀት ለመቆጣጠር እንደሚያስችል ሚስተር መሐመድ አሊ ዬሱፍ አስታውቀዋል።<br />
<br />
ኤርትራ በማን አለብኘነት የጂቡቲን ድንበር ጥሳ የገባችው ስትራቴጂያዊ ጠቀሜታ ያለውን የራስ ዱመራ አካባቢን ለመያዝ ካላት ፍላጎት መሆኑንና ኤርትራ የአገራቸውን አንድነትና ልአላዊነት መድፈሯን አመልክተዋል።<br />
<br />
እንደዜና ምንጩ ዘገባ፤ የኤርትራ ጦር ወደ ጂቡቲ ድንበር በመዝለቅ በብዙ መቶ ሜትሮች የሚቆጠር ምሽግ በመቆፈር ላይ ነው።<br />
<br />
ጂቡቲ የድንበር ፍጥጫውን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ባቀረበችው ግብዣ መሰረት የአረብ ሊግ የሰላምና ፀጥታ ምክር ቤት አስቸኳይ ጉባኤ በማካሄድ የሊጉ ዋና ፀሐፍ ሚስተር አመር ሙሳ ጉዳዩን የሚያጣራ አንድ ቡድን ወደ አካባቢው እንዲልኩ ከውሳኔ ላይ መድረሱን ዘገባው አመልክቷል።<br />
<br />
የአፍሪካ ህብረት በበኩሉ የድንበር ውዝግቡን ሁለቱ አገራት በሰላማዊ ሁኔታ በውይይት እንዲፈቱ ባለፈው ሳምንት ጥሪ ማስተላለፉን ዘገባው አብራርቶ ኤርትራ በበኩሏ ጦሯ የጂቡቲን ድንበር ጥሶ እንዳልገባ አስተባብላለች።]]></description>
            <link>http://www.waltainfo.com/AmNews/2008/May/07May08/46535.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">5AADECEE-1D16-11DD-BF19-000393197FB0-6660-000000808372F998-FFA</guid>
            <pubDate>Thu, 08 May 2008 11:50:58 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>እንግሊዝ ለኢትዮጵያ የ2 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር እርዳታ ሰጠች</title>
            <description><![CDATA[አዲስ አበባ ሚያዝያ 30/2000/ዋኢማ/ ኢትዮጵያ የምዕተ ዓመቱን የልማት ግብ ለማሳካት የምታደርገውን ጥረት የሚረዳ 2 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር እርዳታ የእንግሊዝ ዓለም አቀፍ የልማት መምሪያ መስጠቱን አስታወቀ።<br />
<br />
ትናንት በኤምባሲው ፅህፈት ቤት የዓለም አቀፍ መምሪያ ኃላፊ ሚስተር ፖል አክሮይድ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ እንዳስታወቁት፤ አገሪቱ የምዕተ ዓመቱን የልማት ግብ ለማሳካት የሚረዳትና ለቀጣዩ አንድ ዓመት የሚያገለግል 2 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር ተስጥቷታል።<br />
<br />
የገንዘብ እርዳታው በዋናነት የሚውለው በአገሪቱ ለሚከናወኑ የድህነት ቅነሳ ፕሮግራሞች መሆኑን ጠቅሰው፤ ከነዚህ መካከል ግብርና፣ ጤና፣ ትምህርት እንዲሁም ውሃና ሳኒቴሽን ዋና ዋናዎቹ መሆናቸውን ገልፀዋል።<br />
<br />
ኢትዮጵያ እ.ኤ.አ ከ2000 ጀምሮ እድገት እያስመዘገበች መሆኑን ኃላፊው ገልፀው፤ የኢኮኖሚ ዕድገቱም ላለፉት 4 ዓመታት ከ10 በመቶ በላይ ማስመዝገብ መቻሏንና ባለፉት 10 ዓመታት የድህነት መጠኑ ከ46 ወደ 36 በመቶ መቀነሱንም አስታውሰዋል።<br />
<br />
በአገሪቱ በተለያዩ ዘርፎች ለውጥ እያየን ነው ያሉት ኃላፊው በትምህርት፣ በውሃና ሳኒቴሽን እንዲሁም በጤናው ዘርፍ አመርቂ ውጤት እያስመዘገበች መሆኑን ገልፀዋል።<br />
<br />
በመሆኑም የምዕተ ዓመቱን የልማት ግብ ለማሳካት ተጨማሪ ዕርዳታ እንደሚያስፈልጋት ገልፀው፤ የእንግሊዝ መንግስት ዛሬ የሰጠው 2 ነጥብ 5 ቢሊየን ብርም መንግስታችን አገሪቱ የምዕተ ዓመቱን የልማት ግብ ለማሳካት የምታደርገውን ጥረት ለመደገፍ ቁርጠኛ መሆኑን ያመለክታል ብለዋል።<br />
<br />
ላለፉት 4 ዓመታት የዓለም አቀፍ ልማት መምሪያ በኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ግንባታ እንዲጠናከር፣ የትምህርት፣ ጤና፣ ግብርና፣ ውሃና ሳኒቴሽን አገልግሎት እንዲስፋፋ ድጋፍ ሲሰጥ መቆየቱን ጠቅሰው፤ ዋናው ትኩረታቸው መሰረታዊ አገልግሎቶችን ማዳረስ እንደነበር አስረድተዋል።<br />
<br />
በተለይ ደግሞ ባለፉት ሁለት ዓመታት መንግስታቸው 2 ነጥብ 7 ቢሊየን ብር ድጋፍ ማድረጉን ገልፀው፤ በገንዘቡ 6 ነጥብ 5 ሚሊየን የአልጋ አጎበሮችን፣ የወባ መድሃኒትና የወሊድ መከላከያ ገዝቶ ማከፋፈሉንና የትምህርትና የጤና ሙያተኞችን የተለያዩ ክፍያዎች ለመሸፈን ማስቻሉን አመልክተዋል።<br />
<br />
በኢትዮጵያ የእንግሊዝ አምባሳደር ኖርማን ሊንግ በበኩላቸው የእንግሊዝ መንግስት ኢትዮጵያ ድህነትን ለመቀነስ የምታደርገውን ጥረት ለመደገፍ ቁርጠኛ አቋም እንዳለው ገልፀው፤ ዘንድሮ የተሰጠው ድጋፍ በእጥፍ ማደጉ ይህን ያመላክታል ብለዋል።<br />
<br />
ለኢትዮጵያ የምናደርገው ድጋፍ ከስድስት ዓመት በፊት 180 ሚሊየን ብር እንደነበረ አምባሳደሩ አስታውሰው ድጋፉ ዘንድሮ ወደ 2 ነጥብ 5 ቢሊየን አድጓል ብለዋል፡፡]]></description>
            <link>http://www.waltainfo.com/AmNews/2008/May/08May08/46562.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">41C2DEC8-1D16-11DD-BF19-000393197FB0-6660-0000008030AE7698-FFA</guid>
            <pubDate>Thu, 08 May 2008 11:49:33 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>የአፍሪካ አገራት የወጣቶችን ጉዳይ እንደ አንድ አጀንዳ ይዘው መወያየት መቻላቸው ለወጣቱ የሰጡትን ትኩረት ያሳያል ተባለ</title>
            <description>&lt;FONT color=&quot;#FF0033&quot;&gt;አዲስ አበባ&lt;/FONT&gt; ጥር 6/2000/ዋኢማ/ &lt;U&gt;የአፍሪካ አገራት የወጣቶችን &lt;/U&gt;ጉዳይ እንደ አንድ አጀንዳ ይዘው መወያየት መቻላቸው የአፍሪካ መንግስታት ለጉዳዩ የሰጡትን ከፍተኛ ትኩረት እንደሚያሳይ በስብሰባው ላይ ተካፋይ የሆኑ የተለያዩ አገራት ተወካዮች ገለጹ።&lt;BR&gt;
&lt;BR&gt;
በወጣቶች ላይ ትኩረት ሰጥቶ የሚነጋገረው የአፍሪካ ህብረት ሚኒስትሮች ቋሚ ኮሚቴ 2ኛ መደበኛ ጉባኤ ላይ ተሳታፊ ከሆኑት የተለያዩ የአፍሪካ አገራት ተወካዮች መካከል አንዳንዶቹ ለዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል ዛሬ አንደገለጹት፣  የአፍሪካ ወጣቶች በማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ዘርፎች ላይ አተኩረው መሳተፍ መቻላቸው ለአህጉሪቱ እድገትና ብልጽግና የጎላ አስተዋጽኦ አለው።</description>
            <link>http://www.waltainfo.com/AmNews/2008/Feb/14Feb08/43605.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">37CB69FE-DBC3-11DC-9D61-000393197FB0-494-00000093EA009B8B-FFA</guid>
            <pubDate>Fri, 15 Feb 2008 07:43:22 -0500</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>ኢትዮጵያ ውስጥ አቅጣጫን የሚጠቁም የመረጃ አገልግሎት ቴክኖሎጂ ይፋ ሆነ</title>
            <description><![CDATA[አዲስ አበባ, ጳጉሜን 1 ቀን 1999 (አዲስ አበባ) - ኢትዮጵያ ውስጥ ለተጓዦችና ለአገር ጎብኝዎች አቅጣጫዎችን በመጠቆም የመረጃ አገልገሎት የሚሰጥ ''ግሎባል ፖዚሽ ሶሉሽን'' /ጂፒኤስ/ የተባለ አዲስ ቴክኖሎጂ ተግባራዊ ሊሆን ነው፡፡ 27 ሺህ መንደሮችን፣ ከተሞችንና ወረዳዎችንና ያካተተ መሆኑን የፈጠራው ባለቤት ገለጹ፡፡<br>
ይህንኑ ቴክኖሎጂ በሸራተን አዲስ በተግባር ሲሞከር የቱሪዝምና የባህል ሚኒስተሩ አምባሳደር ሙሐመድ ዲሪር እንደገለጹት የዚህ አይነቱ ዘመናዊ የመረጃ ቴክኖሎጂ ኢትዮጵያ ውስጥ ተግባራዊ መሆኑለቱሪስቶች ጠቃሚ ነው ፡፡<br>
<br>
የመረጃ መሳሪያው በተለይ ለተጓዦችና ለቱሪስቶች ወደሚፈልጉበት ለመሄድና አግልግሎት ለማግኘት ለሚያደርጉት ጥረት ጠቀሜታው ከፍተኛ መሆኑን አምባሳደር መሐመድ ጠቁመዋል፡፡<br>
<br>
በኢትዮጵያ ብዛት ያላቸው የቱሪስት መስህቦች በተለያዩ ከተሞችና አካባቢዎች ቢገኙም ሃብቶቹ የሚገኙበትን ትክክለኛ ስፍራ በካርታም ሆነ በሌላ መረጃ ለተጓዦች አቅጣጫ የሚያመለክት በቂ መረጃ አለመኖሩን ተናገረዋል፡፡<br>
<br>
በተለያዩ የዓለም ክፍሎች የጂፒኤስ አቅጣጫ ጠቋሚ መሳሪያ ከቱሪስት መስህቦች በተጨማሪ የአገልገሎት መስጫ ተቋማትን አድራሻና አቅጣጫ በማመላከት ረገድ አግር ጎብኚዎች እንዳይቸገሩ እንደሚያደርግም አስታውቀዋል፡፡<br>
<br>
የፈጠራው ባለቤት አቶ አካሉ ዓለሙ እንደጠቆሙት ቴክኖሎጂው ኢትዮጵያ ውስጥ አዲስና ለመጀመሪያ ጊዜ ተግባር ላይ የዋለ ነው፡፡<br>
<br>
መሳሪያው በሳተላይት የሚታገዝና ኢትዮጵያውስጥ የሚገኙ 27 ሺህ መንደሮች ፣ወረዳዎችንና ከተሞችን በጉዞ ወቅት የሚያመላክት መሆኑን ገለጸው አንድ አገልግሎት ፈላጊ ተጓዥ ካለበት ቦታ ሆኖ በቅርብ ርቀት ካለው ከተማ ምንአይነት አገልግሎት ማግኘት እንደሚችል በቀላሉ ማወቅይቻለዋል ብለዋል፡፡<br>
<br>
የኢትዮጵያን ተፈጥሯዊና ታሪካዊ ሥፍራዎችን ጨምሮ የትራንሰፖርት ድርጅቶች፣የነዳጅ ማደያዎች ፣የሆቴሎች፣ የሬስቶራንቶች፣የባንክቤቶች እና ሌሎች ጠቃሚ መረጃዎችን መሳሪያው የሚያቀርብ መሆኑንና ወደፊትም እየተሻሻለ እንደሚሄድ ተናግረዋል፡፡፡]]></description>
            <link>http://www.ena.gov.et/AmharicNews/2007/Sep/06Sep07/36948.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">9F161676-5C74-11DC-BDFF-000393197FB0-618-00000153FFA0238B-FFA</guid>
            <pubDate>Thu, 06 Sep 2007 08:28:50 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>የሚሌኒየሙን በአል ለማክበር ከተለያዩ አለማት ለመጡ እንግዶች ደማቅ አቀባበል ተደረገ</title>
            <description><![CDATA[አዲስ አበባ, ነሐሴ 30 ቀን 1999 (አዲስ አበባ) - አዲሱን የኢትዮጵያ ሚሌኒየም በአል ለማክበር ከተለያዩ አለማት ከ500 በላይ ኢትዮጵያውያን፣ ትውልድ ኢትዮጵያውያንና የውጭ አገራት ዜጎች ትናንት ማምሻውን አዲስ አበባ ገብተዋል፡፡<br>
ለእንግዶቹ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ የፈረሙበት የእንኳን ደህና መጣችሁ የመልካም ምኞች መግለጫ ካርድና አበባ ተበርክቶላቸዋል፡፡<br>
<br>
ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ በመልካም ምኞት መግለጫቸው ላይ እንዳሰፈሩት ኢትዮጵያ ተስፋ ሰጪ በሆነ የልማት ጎዳና ላይ ትገኛለች፡፡<br>
<br>
በአሉን ለማክበር የምትመጡ ኢትዮጵያውያን ሙያዊና ቁሳዊ እገዛ ከታከለበት ደግሞ ኢትዮጵያ ይበልጥ ትበለጽጋለች ብለዋል፡፡ ለኢትዮጵያ እድገትም የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ ለእንግዶቹ ግብዣ አቅርበዋል፡፡<br>
<br>
ትናንት ማምሻውን አዲስ አበባ ከገቡት እንግዶች መካከል የአሜሪካ ሚኖሶታ ነዋሪ የሆነው ዳኛቸው ጉደታ እንደገለጸው በአሉን ለማክበር ወደ አገሩ በመምጣቱ ተደስቷል፡፡ ለብሄራዊ ሚሌኒየም ጽህፈት ቤት 30 የሚጠጉ መጽሃፍትን በስጦታ ለማበርከት መዘጋጀቱንም አመልክቷል፡፡<br>
<br>
ሁሉም ያለፈውን ጊዜ በመርሳት አዲሱን ሚሌኒየም በመቻቻልና በመደጋገፍ ሊያከበረው እንደሚገባ አሳስቧል፡፡<br>
<br>
ሌላው የአሜሪካ የሜይን ፖርትላንድ ነዋሪ የሆኑት አቶ አረፍአይኔ የኔነህ በበኩላቸው ወደ ኢትዮጵያ የመጡት የሚሌኒየም በአሉን ለማክበር ነው፡፡ በኢትዮጵያ ቆይታቸውም የተለያዩ የኢንቨስትመንት አማራጮችን እንደሚያጠኑ ገልጸዋል፡፡<br>
<br>
ላለፉት 12 አመታት በቦስተን ነዋሪ የሆነችው ሙሉ ጥላሁን ለበአሉ ወደ አገሯ በመመለሷ መደሰቷን ገልጻ ሁሉም ኢትዮጵያዊ የሚሌኒየሙን አጋጣሚ በመጠቀም ለለውጥ እንዲነሳ ጥሪ አቅርባለች፡፡<br>
<br>
ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ለሚሌኒየሙና ከውጭ ለሚመጡ እንግዶች ልዩ ትኩረት በመስጠት በፊርማቸው ያበረከቱት የመልካም ምኞት መግለጫ ካርድ ልዩ ስሜት እንዳሳደረባት ገልጻለች፡፡ ይህም በኢትዮጵያ ታሪክ የመጀመሪያው መሆኑን ጠቁማለች፡፡<br>
<br>
ለእንግዶቹ በቦሌ አለም አቀፍ አውሮፕላን ጣቢያ በመገኘት ደማቅ አቀባበል ያደረጉላቸው የአዲስ አበባ ሚሌኒየም ጽህፈት ቤት ዋና ዳይሬክተር አቶ ኪሮስ ሃይለ ስላሴ እንደገለጹት ጽህፈት ቤቱ ለእንግዶቹ የሚያደረገው አቀባበል እስከ መጪው ሰኔ ወር 2000 ዓም ድረስ ይቀጥላል፡፡]]></description>
            <link>http://www.ena.gov.et/AmharicNews/2007/Sep/05Sep07/36774.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">B928ECD6-5C74-11DC-BDFF-000393197FB0-618-00000154563B21DC-FFA</guid>
            <pubDate>Thu, 06 Sep 2007 08:29:13 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>በሚሊኒየሙ የብሄር ብሄረሰቦችን መልካም ገጽታ በአገር ውስጥና በዓለም ዙሪያ ማስተዋወቅ በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ ያተኮረ አውደ ጥናት ነገ ይጀመራል</title>
            <description><![CDATA[በሚሊኒየሙ የብሄር ብሄረሰቦችን መልካም ገጽታ በአገር ውስጥና በዓለም ዙሪያ ማስተዋወቅ በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ ያተኮረ አውደ ጥናት ነገ ይጀመራል<br>
አዲሰ አበባ, ሚያዝያ 8 ቀን 1999 (አዲስ አበባ)<br>
በአዲሱ የኢትዮጵያ ሚልኒየም የብሄር ብሄረሰቦችን መልካም ገጽታ ለአገር ውስጥና ለዓለም ሕዝብ ማስተዋወቅ በሚቻልበት ጉዳይ ላይ የሚመክር የግንዛቤ ማሳደጊያ አውደ ጥናት ነገ እንደሚጀመር የፌዴሬሽን ምክር ቤት ጽህፈት ቤት አስታወቀ፡፡<br>
<br>
በጽህፈት ቤቱ የፕሬስ፣ የሕዝብ ግንኙነትና የቃለ ጉባኤ ማደራጃ አገልግሎት ኃላፊ አቶ አለምነህ ረጋሣ ዛሬ ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጹት አውደ ጥናቱ የተዘጋጀው በመላው አገሪቱ ያሉ የሥነ ጥበብ፣ የቋንቋና የመገናኛ ብዙኃን ተቋማት የብሄር ብሄረሰቦችን እኩልነትና መልካም ገጽታ ለአገር ውስጥና ለዓለም ኅብረተሰብ ለማሳወቅ በሚችሉበት አካሄድ ላይ ግንዛቤ ለመፍጠር ነው፡፡<br>
<br>
በአዲሱ ሚሌኒየም ለኢትዮጵያ ብሄር ብሄረሰቦች ትኩረት መስጠትና ባለፉት ሥርዓቶች ተረስተው የቆዩ ብሄረሰቦችን የማስተዋወቅ ተግባር ለማከናወን በሚቻልበት ጉዳይ ላይ መምከር የአውደ ጥናቱ ዓላማ መሆኑን ኃላፊው ተናግረዋል፡፡<br>
<br>
አውደ ጥናቱ የብሄር ብሄረሰቦችን ጉዳይ ሁሉም አካላት በባለቤትነት እንዲመለከቱት በማድረግ የልምድ ልውውጥ መድረክ እንደሚፈጥር አስታውቀዋል፡፡<br>
<br>
በአውደ ጥናቱ ላይ የሥነ ጥበባትና የመገናኛ ብዙኃን ተቋማት የብሄር ብሄረሰቦችን ማንነት ከማንፀባረቅ አኳያ የሚጠበቅባቸውን ሚና የሚያስገነዝቡ ጥናታዊ ጽሁፎች ይቀርባሉ፡፡<br>
<br>
እንደ ኃላፊው ገለጻ በአውደ ጥናቱ የሥነ ጥበባት፣ የቋንቋና የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች የኢትዮጵያ ብሄር ብሄረሰቦችና ሕዝቦችን በማቀራረብ ረገድ ሊጫወቱት በሚገባ ሚናና ማበርከት የሚችሉት አስተዋጽኦ ከፍተኛ በመሆኑ ስለ አፈጻጸሙ የጋራ ምክክር ይደረጋል፡፡<br>
<br>
''የኢትዮጵያ ብሄር ብሄረሰቦች ገጽታ በሚልኒየም የሥነ ጥበባት፣ የቋንቋና የመገናኛ ብዙኃን ሚና'' በሚል ርዕስ በተዘጋጀውና ለአንድ ቀን በሚቆየው አውደ ጥናት ጥሪ የተደረገላቸው ሚኒስትሮች፣ የተወካዮችና የፌዴሬሽን ምክር ቤት ቋሚ ኮሚቴ አባላት፣ የመገናኛ ብዙኃን ኃላፊዎች፣ ታዋቂ ግለሰቦች፣ የቴአትር፣ የሙዚቃና የሥዕል ባለሙያዎች እንዲሁም ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተውጣጡ ከ200 በላይ ባለሙያዎች ተሳታፊ ይሆናሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡]]></description>
            <link>http://www.ena.gov.et/AmharicNews/2007/Apr/16Apr07/22575.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">A8938668-EC42-11DB-9235-000393197FB0-676-00000088693D0696-FFA</guid>
            <pubDate>Mon, 16 Apr 2007 13:49:15 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>ለሚሊኒየም በአል ወደ የኢትዮጵያ ለሚመጡ የውጭ አገራት እንገዶችን በሚገባ ለማስተናገድ እንዲቻል ለሰራተኞች ስለጠና ተሰጠ-ዋቢ ሸበሌ ሆቴሎች ድርጅት</title>
            <description><![CDATA[ለሚሊኒየም በአል ወደ የኢትዮጵያ ለሚመጡ የውጭ አገራት እንገዶችን በሚገባ ለማስተናገድ እንዲቻል ለሰራተኞች ስለጠና ተሰጠ-ዋቢ ሸበሌ ሆቴሎች ድርጅት<br>
አዲስ አበባ, ሚያዝያ 8 ቀን 1999 (አዲስ አበባ)<br>
መጪውን የሚሊኒየም በአል ለማክበር ወደ የኢትዮጵያ የሚመጡ የውጭ አገራት እንገዶችን በሚገባ ለማስተናገድ የዋቢ ሸበሌ ሆቴሎች ድርጅት ለሰራተኞቹ የሚሰጠው የመጨረሻው ስልጠና ዛሬ በአዲስ አበባ ተጀመረ፡፡<br>
<br>
የድርጅቱ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ አየለ ዘውዴ ዛሬ ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጹት ድርጅቱ በሁሉም ቅርንጫፍ ሆቴሎቹ በመስራት ላሉ ለሰራተኞች የሚሰጠው ስልጠና አላማ ለሚሊኒየሙ በአል ወደ አገር ውስጥ ለሚገቡ እንግዶች የተሟላ መስተንግዶ ለማቅረብ እንዲቻል ነው፡፡<br>
<br>
ስልጠናው ለሰራተኞቹ በመደበኛነት በያመቱ የሚሰጥ ቢሆንም በቅርቡ ለሚከበረው የኢትዮጵያ ሚሊኒየም በአል አስተማማኝ መስተንግዶ ለመስጠትና የአገሪቱን መልካም ገጽታና እንግዳ ተቀባይነት ይበልጥ ለማጉላት ለሰራተኞቹ የጠለቀና ሰፋ ያለ ትምህርት በመሰጠት ላይ ይገኛል፡፡<br>
<br>
ድርጅቱ ለእንግዶቹ የሚሰጠውን መስተንግዶ ይበልጥ የተቀላጠፈ ለማድረግ በወንዶገነት፣በላንጋኖ፣በባሌና በሶደሬ ለሚሰሩ ሰራተኞቹ የተሰጠው ስልጠና መጠናቀቁንና ዛሬ አዲስ አበባ በሚገኘው የድርጅቱ ሆቴል የተጀመረው ስልጠናም የዚሁ አካል መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡<br>
<br>
ድርጅቱ ለ10 ቀናት በሚሰጠው ስልጠና ላይ 560 የሚሆኑ ሰራተኞቹ መሳተፋቸውንና ስልጠናውም ስለ እንግዳ አያያዝና አቀባበል በወጪና ገቢ አያያዝ እንዲሁም አጠቃላይ ከደንበኞች ጋር ስለ ሚደረግ ግንኙነት እነደሚያተኩር ጠቁመዋል፡፡<br>
<br>
ድርጅቱ ለበአሉ ለሚመጡ እንግዶች የሚሰጠውን አገልግሎት ይበልጥ ለማሻሻልም ያሉትን የምግብ ማደረጃ ክፍሎች፣ምግብ ቤቶች፣ቡና ቤቶችና መኝታ ክፍሎች የማደስና የማሻሻል ተግባራት በተጠናከረ ሁኔታ በማከናወን ላይ እንደሚገኝም ገልጸዋል፡፡<br>
<br>
በሶደሬ፣ላንጋኖና ወንዶገነት በሚገኙ መዝናኛ ቦታዎች ላይ የአልጋ ጥበት እንዳይፈጠር በርካታ የማደሪያ ድንኳኖች እየተዘጋጁ መሆናቸውን አስረድተዋል፡፡<br>
<br>
በሶደሬ ከ200 በላይ እንግዶችን ማሳረፍ የሚችሉ 100 ድንኳኖች በላንጋኖም ተመሳሳይ ቁጥር ያላቸው ድንኳኖችን ለማዘጋጀት ከፍተኛ እንቅስቃሴ በመደረግ ላይ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡]]></description>
            <link>http://www.ena.gov.et/AmharicNews/2007/Apr/16Apr07/22537.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">9AC57694-EC42-11DB-9235-000393197FB0-676-000000883B6261F2-FFA</guid>
            <pubDate>Mon, 16 Apr 2007 13:48:17 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>የዓለም ባንክ በናይል ተፋሰስ አገራት ለሚካሄደው የሃይድሮ ፓውር ግንባታ 13 ነጥብ 1 ሚሊዮን ዶላር ሰጠ</title>
            <description><![CDATA[የዓለም ባንክ በናይል ተፋሰስ አገራት ለሚካሄደው የሃይድሮ ፓውር ግንባታ 13 ነጥብ 1 ሚሊዮን ዶላር ሰጠ<br>
አዲስ አበባ, ሚያዝያ 8 ቀን 1999 (አዲስ አበባ) - የዓለም ባንክ በናይል ተፋሰስ አገራት ለሚካሄደው አዲስ የሃይድሮ ፓውር ግንባታ 13 ነጥብ 1 ሚሊዮን ዶላር መስጠቱን አስታወቀ፡፡<br>
ፕሮጀክቱን በገንዘብ የሚደግፈው የዓለም ባንክ ለመጀመሪያው ምእራፍ የሃይል ስራ 7 ነጥብ 71 ሚሊዮን ዶላር፤ ለሁለተኛው ደግሞ 5 ነጥብ 39 ሚሊዮን ዶላር መድቧል፡፡<br>
<br>
የተፋሰሱ አገራት በክፍለ አህጉራዊ የኤሌክትሪክ ኀይል ንግድ ፕሮጀክት አማካኝነት ለአባል አገራቱ አገልግሎት የሚሰጥና በአካባቢው ተፎካካሪ የሆነ የሃይል ገበያን ለመፍጠር የሚያስችል የሃይል ማመጫ ለመገንባት በመንቀሳቀስ ላይ ናቸው፡፡<br>
<br>
ይህ ፕሮጀክት በአራት ዓመታት ጊዜ ውስጥ ለማከናወን ከተያዙት እቅዶች መካከል አንዱ ሲሆን ዓላማውም የናይል ተፋሰስ የሃይል ፎረምን በመመስረት በአካባቢው አገራት የሃይል ገበያ ልማት ትብብርን ማጠናከር መሆኑን ዘ ኢስት አፍሪካን ጋዜጣ ትናንት ዘግቧል፡፡<br>
<br>
የናይል ተፋሰስ ክፍለ አህጉራዊ የኤሌክትሪክ ሃይል ንግድ ፕሮጀክት ሊቀመንበር ዶክተር ሃጂ ሴምቦጃ እንደተናገሩት የፕሮጀክቱ ዓላማ በተፋሰሱ አገራት ውስጥ ዘርፈ ብዙ የተቀናጀ የሀይል ልማት ተግባራትን በማከናወንና የውሃ አስተዳደር ስርዓትን በመፍጠር አስተማማኝና በዝቅተኛ ዋጋ የኤሌክትሪክ አቅርቦትን ማቅረብ ነው፡፡<br>
<br>
በናይል ተፋሰስ አካባቢ አገራት በአሁኑ ወቅት ያለው ዓመታዊ አማካይ የኤሌክትሪክ ኀይል ፍጆታ ከ 6 ነጥብ 5 ኪሎ ዋት ያነሰ መሆኑንም አስረድተዋል፡፡<br>
<br>
ፕሮጀክቱ እንደ አውሮፓ አቆጣጠር በ1999 ተቀርፆ ተግባራዊ የተደረገው በናይል ተፋሰስ ኢኒሽዬቲቭ ፕሮግራም አማካኝነት ሲሆን ኢኒሽዬቩም ኢትጵያን ጨምሮ ብሩዲን፣ ዲመራሲያዊ ኮንገ ሪፐብሊን፣ ግብፅን፣ ኬንያን፣ ርዋንዳን፣ ሱዳንን፣ ታንዛኒያንና ኡጋንዳን አሰባስቧል፡፡<br>
<br>
ፕሮጀክቱ የተፋሰሱ አባል አገራት የድንበር ተሻጋሪ የተፈጥሮ ኀብታቸውን አካባቢ አገራት መካከል የሚኖረውን ውጥረት በማርገብ ተቀራርቦ መስራትን ለማጠናከር ከፍተኛ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ሲሉ የፕሮጀክቱ ባለሙያዎች ይናገራሉ፡፡<br>
<br>
በሌላ በኩል ኬንያንና ኡጋንዳን፣ ኡጋንዳንና ርዋንዳን፣ ርዋንዳንና ብሩንዲን፣ በኤሌክትሪክ ኀይል ለማገናኘት የሚያስችለው ዝርዝር ጥናት በመካሄድ ላይ ነው፡፡]]></description>
            <link>http://www.ena.gov.et/AmharicNews/2007/Apr/16Apr07/22543.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">5DD1E73E-EC42-11DB-9235-000393197FB0-676-0000008770EE073E-FFA</guid>
            <pubDate>Mon, 16 Apr 2007 13:47:54 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>የምእራቡ ዓለም ሚዲያዎች ኢትዮጵያ ያላትን እውነተኛና ትክክለኛ ገጽታ ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ በሚገባ ማስተጋባት ይባቸዋል</title>
            <description><![CDATA[የምእራቡ ዓለም ሚዲያዎች ኢትዮጵያ ያላትን እውነተኛና ትክክለኛ ገጽታ ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ በሚገባ ማስተጋባት ይባቸዋል<br>
አዲስ አበባ, ሚያዝያ 8 ቀን 1999 (አዲስ አበባ) - የምእራቡ አለም ሚዲያዎች ኢትዮጵያ ያላትን እውነተኛና ትክክለኛ ገጽታ ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ በሚገባ ሊገለጹ እንደሚያስፈልግ የባህልና ቱሪዝም ሚኒስትሩ አምባሳደር መሃሙድ ድሪር አሳሰቡ፡፡<br>
የኢትዮጵያን ሚሊኒየም በአልና የኢትዮጵያን ታሪክና ባህል ለማስተዋወቅ ከሶሰት የአውሮፓ አገሮች ለመጡ ጋዜጠኞች ትናንት ምሽት በሸራተን አዲስ የኢትዮጵያን ወቅታዊ ሁኔታና በመጪው የሚሊኒየም በአልን በተመለከተ ማብራሪያ በሰጡበት ወቅት አምባሳደር መሃሙድ ድሪር እንዳሉት በምእራቡ አለም ሚዲያዎች የኢትዮጵያን እውነተኛና ትክክለኛ ገጽታ ከመዘገብ ይልቅ በአሉታዊ ጎኑን በማጉላት ማቅረባቸው አገሪቱ ውጭው አለም ያላት ገጽታ በተሳሳተ አቅጣጫ እንዲተረጎም አድርጓል፡፡<br>
<br>
በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ በርካታ አዎንታዊ ሁኔታዎች እንዳሉና አገሪቱም በመልካም የእድገት ጎዳና ላይ የምትገኝ በመሆኗ ይህን ሃቅና እውነታ አለም አቀፉ ማህበረሰብ በሚገባ መገንዘብ አለበት ብለዋል፡፡<br>
<br>
የእምራቡ አለም ጋዜጠኞችና ሚዲያዎችም በኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት ያለው እውነታ የተለየና አዎንታዎ በመሆኑ ከዚህ ቀደም ስለአገሪቱ የነበራቸውን የተሳሳተ አመለካከት የሚያስተካክሉበት ጊዜ ትክክለኛው ወቅት አሁን ነው ብለዋል፡፡<br>
<br>
የኢትዮጵያ ሚሊኒየም ጽሀፈት ቤት ዋና ዳይሬከተር አቶ ስዩም በረደድ በበኩላቸው ሶስተኛው የኢትዮጵያ ሚሊኒየም በአል አገሪቱ በሁሉም መስክ እድገትና ህዝቦቿም በጋራና በመተጋገዝ ለአገሪቱ እድገት የሚሰሩበት ወቅት ይሆናል ብለዋል፡፡<br>
<br>
በዓሉ ኢትዮጵያ የበርካታ ባህሎችና ብሄር ብሄረሰቦች አገር መሆኗን፣ የተለያዩ ሃይማኖቶች በመቻቻልና በመፈቃቀር የሚኖሩባትና ይህንንም እውነታ በመጪው የሚሊኒየም በዓል ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ በይፋ የምታሳይበት መልካም አጋጣሚ እንደሚሆን ተናግረዋል፡፡<br>
<br>
ኢትዮጵያዊያን ከመለያየት ይልቅ በአንድነትና በጋራ ለአገራቸው የወደፊት ራእይና እድገት በጋራ የሚያቅዱበት ጊዜ እንደሚሆንም አብራርተዋል፡፡<br>
<br>
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ግርማ ዋቄ አየር መንገዱ የኢትዮጵያን ሚሊኒየም በዓል ለውጭው አለም ለማስተዋወቅ ከአሜሪካ፣ ከአውሮፓና ከተለያዩ አገራት ጋዜጠኞችን በመጋበዝ የአገሪቱን ባህላዊ እሴቶችና ታሪኮች በሚገባ እንዲገነዘቡ በማድረግ ላይ እንደሚገኝ ጠቁመዋል፡፡<br>
<br>
አየር መንገዱ በትናንትናው እለት ወደ ኢትዮጵያ በመጋበዝ ያስመጣቸው 12 ጋዜጠኞች ከቤልጂየም፣ ኔዘርላንድና ሉክሰምበርግ የተውጣጡ መሆናቸውንም ጠቅሰዋል፡፡<br>
<br>
ጋዜጠኞቹ ለ12 ቀናት በኢትዮጵያ በሚያደርጉት ቆይታ በተለያዩ ክልሎች በመዘዋወር የአገሪቱን ተፈጥሮአዊና ሰው ሰራሽ ታሪካዊ መስሀቦች እንደሚጎበኙ አመልክተው ወደ መጡበት አገር ሲመለሱም ያዩትንና ያታዘቡትን እውነታና በመዘገብ ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ያሳውቃሉ ብለው እንደሚገምቱ ገልጸዋል፡፡]]></description>
            <link>http://www.ena.gov.et/AmharicNews/2007/Apr/16Apr07/22526.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">FFC1534D-EC41-11DB-9235-000393197FB0-676-00000086387CA396-FFA</guid>
            <pubDate>Mon, 16 Apr 2007 13:46:12 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>ዩኒቨርስቲው በመጪው ዓመት አዳዲስ የዶክርትሬትና የማስተርስ ዲግሪ መርሃግብሮችን ሊከፍት ነው</title>
            <description><![CDATA[ዩኒቨርስቲው በመጪው ዓመት አዳዲስ የዶክርትሬትና የማስተርስ ዲግሪ መርሃግብሮችን ሊከፍት ነው<br>
አዲስ አበባ ሚያዝያ 8/1999 የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመጪው የትምህርት ዘመን የዶክትሬትና የማስተርስ ዲግሪ ስልጠና ፕሮግራሞችን ጨምሮ በርካታ አዳዲስ የምርምርና የትምህርት ማዕከላትን ለመክፈት የሚያስችል ዝግጅት በማድረግ ላይ መሆኑን አስታወቀ።<br>
<br>
በዩኒቨርስቲው የዓለም አቀፍ ጉዳዮች ተባባሪ ምክትል ፕሬዚዳንት፣ የሪፎርምና የስትራቴጂክ ዕቅድ ዳይሬክተር ዶክተር አብይ ጣሴ ለዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል እንዳስታወቁት፤ በመጪው ጥቅምት ወር የሚጀመሩት አዳዲስ የዶክትሬትና የማስተርስ ዲግሪ ስልጠና ፕሮግራሞችና የምርምር ስራዎች የዩኒቨርስቲውን የቀጣይ አምስት አመት ስትራቴጂክ ዕቅድ መነሻ በማድረግ የተዘጋጁ ናቸው።<br>
<br>
በዶክትሬት ዲግሪ ስልጠና ከሚሰጥባቸው የትምህርት መስኮች መካከል የአካባቢ ልማት፣ የምርምር ልማት ማህበራዊና ስነ ጾታ ትምህርት መስኮች ዋነኞቹ መሆናቸውን ገልፀዋል።<br>
<br>
እነዚህም በዩኒቨርስቲው ሥር በሚቋቋም የልማት ጥናትና ምርምር ኮሌጅ አማካኝነት የሚሰጡ መሆናቸውን ጠቁመዋል።<br>
<br>
በህክምና ዘርፍ ያሉት የፋርማሲ፣ የእንስሳት ህክምናና ሌሎችም የትምህርት ዘርፎችን በማሰባሰብ ራሱን የቻለ አንድ የስልጠናና የምርምር ተቋም እንደሚደራጅ ዶክተር አብይ አመልክተው የንግድ ስራ ኮሌጅና የፋይናንስ ጥናት አካዳሚ የማዋሃድ ተግባርም እንደሚከናን አስረድተዋል።<br>
<br>
በውሃ ቴክኖሎጂ፣ በማህበረሰብ ሳይንስ፣ በኢንፎርማቲክስ፣ በምግብዋስትናና በሌሎች ተያያዥ ዘርፎች ላይ የማስተርስ የስልጠና ፕሮግራም የሚጀመረው ሲሆን በተጓዳኝም በርካታ የምርምር ስራዎች እንደሚካሄዱ አመልክተዋል።<br>
<br>
ከዚህም ሌላ ዩኒቨርስቲው ከሌሎች ዩኒቨርስቲዎች ጋር በመተባበር የሰላምና ደህንነት፣ በፌዴራሊዝምና ፓርላመንታዊ ስርዓት ዙሪያ የማስተርስ ትምህር ለመስጠት አዳዲስ ኢንስቲትዩቶች መቋቋማቸውንና ተቋማቱ የጥናትና ምርምር ስራ ለማካሄድ አጋዥ መሆናቸውን አስታውቀዋል።<br>
<br>
/ለኢቴቪ የዶክተር አብይን ድምፅ ተጠቀሙ/<br>
<br>
"አዳዲስ ኢንስቲትዩሽኖች የተከፈቱ አሉ ወደፊትም ይከፈታሉ ለምሳሌ በሰላምና የደህንነት ተቋም ተቋቁሟል። እናም አንገብጋቢ የሚባሉ ተቋማትን በመክፈት ላይ ነው ያለነው እንግዲህ ይህ ከአገሪቷ እድገት ጋር አብሮ ተጣጥሞ የሚሄድ ነው በሚል ነው ።"<br>
<br>
ተቋማቱ የመንግሥት ፖሊሲዎችና ስትራቴጂዎች ለማስፈፀም የሚያግዝ የሰው ኃይል ለማፍራትና ችግር ፈቺ የምርምር ስራዎችን ለማካሄድ ትልቅ አቅም እንደሚፈጥሩ ዶክተር አብይ አስረድተዋል።<br>
<br>
ዩኒቨርስቲው በቀጣይም ሌሎች አዳዲስ የስልጠናና የምርምር መስኮችን ለመክፈት ሰፊ እንቅስቃሴ በማድረግ ላይ መሆኑን ገልፀው፤ ይህም በቀጣዮቹ ጥቂት አመታት በአገሪቱ ያሉ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ያለባቸውን የሠው ኃይል እጥረት እንደሚያቃልል አብራርተዋል።<br>
<br>
ዩኒቨርሲቲው በተያዘው የትምህርት ዘመን በኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂና በኢንጅነሪንግ የትምህርት ክፍል 40 ሰልጣኞችን በዶክትሬት ዲግሪ መርሃግብር ለመጀመሪያ ጊዜ ተቀብሎ በማሰልጠን ላይ እንደሚገኝ ዶክተር አብይ ተናግረዋል።<br>
<br>
ዩኒቨርስቲው ባስቀመጠው የቀጣይ አምስት ዓመታት ስትራቴጂክ እቅድ መሠረት በማስተርስና በዶክትሬት ዲግሪ በተለያዩ የትምህርት መስኮች አዳዲስ ፕሮግራሞችን መክፈቱን እንደሚቀጥል ዶክተር አብይ መግለጻቸውን ዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል ዘግቧል።]]></description>
            <link>http://www.waltainfo.com/AmNews/2007/Apr/16Apr07/27563.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">EBC17DAB-EC41-11DB-9235-000393197FB0-676-00000085F60EBDB6-FFA</guid>
            <pubDate>Mon, 16 Apr 2007 13:43:34 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>በኢትዮጵያ ያለው ስርዓት ሙስሊሙ ህዝብ ህገ መንግስቱ ያጎናፀፈውን መበት ተጠቅሞ እምነቱን በነፃነት ለመተግበር የሚያስችለው መሆኑ ተገለፀ...</title>
            <description><![CDATA[አዲስ አበባ, ሚያዝያ 2 ቀን 1999 (አዲስ አበባ)<br>
በኢትዮጵያ ያለው ስርዓት ሙስሊሙ ህዝብ ህገ መንግስቱ ያጎናፀፈውን መብት ተጠቅሞ እምነቱን በነፃነት ለመተግበር የሚያስችለው ነው ሲሉ በተለያዩ አገራት የሚኖሩ ሙስሊም ኢትዮጵያንን ያሰባሰበው የልኡካን ቡድን መሪ አስታወቁ፡፡<br>
<br>
በበድር ኢንተርናሽናል የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ፌዴሬሽን አስተባባሪነት በኢትዮጵያ ጉብኝት እያደረገ ያለው የልኡካን ቡድን መሪ አቶ ነጂብ ሙሐመድ ዛሬ ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጹት ዘጠኝ አባላትን የያዘው ቡድን በትናንትናው እለት ከኢትዮጵያ ከፍተኛ ባለስልጣናት ጋር በተናጠል ተገናኝተው በአገሪቱ የእምነት ነፃነት፣ የሃይማኖቶች መቻቻልና ሌሎች ተያያዥ በሆኑ ጉዳዮች ዙሪያ ሰፊ ውይይት አድርገዋል፡፡<br>
<br>
በዚሁ ውይይታቸው በኢትዮጵያ ያለው ስርዓት አመቺና ሙስሊሙ ህብረተሰብም ህገ መንግስቱ በሰጠው መብት ተጠቅሞ መደራጀትና እምነቱን በነፃነት መከወን የሚያስችለው መሆኑን መገንዘባቸውን አመለክተዋል፡፡<br>
<br>
በመላው ዓለም የሚኖሩ ሙስሊም ኢትዮጵያዊያን ከሌሎቹ የአገሪቱ ዜጎች ጋር በመሆን ልማትና አድገት ለማምጣት በሚደረገው ጥረት ውስጥ የሚኖራቸውን ተሳትፎ ማጎልበት በሚቻልበት መንገድ ላይም ውይይት መደረጉን የልኡካን ቡድኑ መሪ ጠቁመዋል፡፡<br>
<br>
ከኢትዮጵያ መንግስት ከፍተኛ ባለስልጣናት ጋር በተደረገ ተከታታይ የደብዳቤ ልውውጥ እውን የሆነው ጉብኝት ዓላማ በኢትዮጵያ ተግባራዊ በተደረገው ህገመንግስታዊ መብት በመጠቀም ሙሰሊሙ ህብረተሰብ ከሌላው ማህበረሰብ ጋር በመሆን በመከባበበርና መተሳሰብ የበለጠ የልማትና የሰላም ተጠቃሚ ማድረግ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ መምከር ነው ብለዋል፡፡<br>
<br>
በመጪዎቹ ቀናትም ከተለያዩ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት ጋር በቡድኑ ጉብኝት ዓላማ ዙሪያ ውይይት የሚደረግ መሆኑንም አቶ ነጂብ ገልፀዋል፡፡<br>
<br>
በድር ኢንተርናሽናል የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ፌዴሬሽን በመላው ዓለም የሚገኙ በብዙ መቶ ሺህ የሚቆጠሩ ሙስሊም ኢትዮጵያዊያንን የሚወክሉ ከ50 ሺህ በላይ አባላት አሉት፡፡<br>
<br>
የልኡካን ቡድኑ የተውጣጣው ከአሜሪካ፣ ከካናዳ፣ ከቤልጂየም፣ ከሳውዲ አረቢያ፣ ከስዊዲንና ከጀርመን ነው፡፡]]></description>
            <link>http://www.ena.gov.et/AmharicNews/2007/Apr/10Apr07/22006.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">6390F162-E78C-11DB-BB94-000393197FB0-421-000000137AD5AEF3-FFA</guid>
            <pubDate>Tue, 10 Apr 2007 14:02:15 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>በአሸባሪነት ተጠርጥረው ኢትዮጵያ ውስጥ በቁጥጥር ሥር የሚገኙ የውጭ ዜጎች ተገቢው የሰብዓዊ መብት አጠባበቅና እንክብካቤ እየተደረገላቸው እንደሆነ ገለጹ...</title>
            <description><![CDATA[አዲስ አበባ, ሚያዝያ 2 ቀን 1999 (አዲስ አበባ)<br>
<br>
በዓለም ዓቀፍ አሸባሪነት ተጠርጥረው በቁጥጥር ሥር የዋሉትና በኢትዮጵያ የሚገኙት የውጭ ዜጎች ተገቢው የሰብዓዊ መብት አጠባበቅ እየተደረገላቸው እንደሆነና አስፈላጊው እንክብካቤ እየተደረገላቸው መሆኑን አስታወቁ፡፡<br>
<br>
በአሸባሪነት ተጠርጥረው በቁጥጥር ሥር የዋሉትና በኢትዮጵያ የሚገኙት የውጭ ዜጎች ትናንትለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት በሰጡት መግለጫ ላይ እንዳመለከቱት በኢትዮጵያ መንግሥት አስፈላጊው እንክብካቤ እየተደረገላቸው ነው፡፡<br>
<br>
በሶማሊያ እንዲሁም በሶማሊያና በኬንያ ድንበር አዋሳኝ አካባቢዎች ከሁለት ወራት በፊት በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን ጠቁመው ወደ ኢትዮጵያ በገቡበት ወቅት ፍርድ ቤት መቅረባቸውንም አስታውቀዋል፡፡<br>
<br>
በአሸባሪነት ተጠርጥረው በቁጥጥር ሥር የዋሉትና የአሜሪካ፣ የስዊድን፣ የሶሪያ፣ የሳኡዲ አረቢያ፣ የቱኒዝያ፣ የሩዋንዳ፣ የታንዛኒያና የኡጋንዳ ዜግነት ያላቸው የውጭ ዜጎች በኢትዮጵያ መንግሥት አስፈላጊው የምግብ የልብስና ሌሎችም መሠረታዊ አቅርቦቶች በሚፈለገው መጠን እየቀረበላቸው መሆኑንም ገልጸዋል፡፡<br>
<br>
በኢትዮጵያ መንግሥት አስፈላጊው የሰብዓዊ መብት ጥበቃ እየተደረገላቸው እንደሆነና የኢትዮጵያ ፖሊሶችም ጥሩ እንክብካቤ እያደረጉላቸው እንደሆነና የሚፈልጓቸውን ነገሮች ሁሉ በወቅቱ እንዲያገኙ እየተደረገ መሆኑ እንዳስደሰታቸውም ተናግረዋል፡፡<br>
<br>
በአሸባሪነት ተጠርጥረው በቁጥጥር ሥር ከዋሉትና በኢትዮጵያ ከሚገኙት የውጭ ዜጎች መካከል የአሜሪካ ዜግነት እንዳለው የገለጸው አሚር ሞሐመድ በቁጥጥር ሥር የዋለው ሶማሊያ ውስጥ እንደሆነ ገልጿል፡፡<br>
<br>
አፕ ሳውንድ 1ኛ ተናጋሪ አሚር ሞሐመድ መግቢያ 0፡18 ሰከንድ "በኢትዮጵያ በጥሩ ሁኔታ ነው ያለነው፡፡ ምንም ችግር የለም፡፡" መውጫ 0፡42 ሰከንድ<br>
<br>
አያቱ ግብጻዊ እንደሆኑና በአሜሪካ ይኖር እንደነበር የገለጸው አሚር ሞሐመድ ወደ ኢትዮጵያ እንደገባ ፍርድ ቤት መቅረቡን ጠቅሶ በኢትዮጵያ እስካሁን ምንም ዓይነት ችግር እንዳላጋጠመውና አስፈላጊው የሰብዓዊ መብት ጥበቃ እየተደረገለት እንደሆነም ተናግሯል፡፡<br>
<br>
የቱኒዝያ ዜግነት እንዳለው የገለጸው አድናን ነጃህ ነጃህ በበኩሉ በቁጥጥር ሥር የዋለው ሶማሊያና ኬንያን በሚያዋስነው የኬንያ ድንበር አካባቢ እንደሆነ አመልክቷል፡፡<br>
<br>
አፕ ሳውንድ 2ኛ ተናጋሪ አድናን ነጃህ ነጃህ መግቢያ 0፡14 ሰከንድ፡ "ከአንድ ወር በፊት ፍርድ ቤት ቀርበናል፡፡ ከጥቂት ቀናት በኋላ ለሁለተኛ ጊዜ ፍርድ ቤት እንቀርባለን፡፡" መውጫ 0፡28 ሰከንድ<br>
<br>
ወደ ኢትዮጵያ ከገባበት ወቅት ጀምሮ ምንም ዓይነት ችግር እንዳለጋጠመውና የኢትዮጵያ ቆይታው ጥሩ እንደሆነም ገልጿል፡፡<br>
<br>
የሩዋንዳ ዜግነት ያለው ሙሂቢታቦ ክሌሜንት ኢብራሂም በበኩሉ በቁጥጥር ሥር የዋለው የሶማሊያና የኬንያ ድንበር አዋሳኝ በሆነው በኬንያ ድንበር እንደሆነ ተናግሯል፡፡<br>
<br>
አፕ ሳውንድ 3ኛ ተናጋሪ ሙሂቢታቦ ክሌሜንት ኢብራሂም መግቢያ 0፡09 ሰከንድ " ሁሉንም ነገር አደንቃለሁ፡፡ ምክንያቱም በጣም ጥሩ ሕዝብ ነው ያለው፡፡ በጣም ጥሩ ማህበራዊ ግንኙነት አለው፡፡ በጣም ጥሩ ሁኔታ ነው ያለው፡፡"መውጫ 0፡18 ሰከንድ<br>
<br>
ኢብራሂም በቁጥጥር ሥር ከዋለ በኋላ ወደ ኢትዮጵያ መምጣቱንና ፍርድ ቤት መቅረቡንም ጠቅሶ በኢትዮጵያ ቆይታው በቂ ምግብ፣ ንጹህ የመጠጥ ውሃና ሌሎችንም አስፈላጊ ነገሮች በወቅቱ እንደሚያገኝ ጠቁሟል፡፡ በኢትዮጵያ ቆይታውም ምንም ዓይነት የሰብዓዊ መብት ጥሰት እንዳላጋጠመውም አስታውቋል፡፡<br>
<br>
ሌላው በቁጥጥር ሥር የዋለውና በሊባኖስ እንደተወለደና የስዊድን ዜግነት እንዳለው የገለጸው ሙኒር አዋድ "በቁጥጥር ሥር የዋልኩት በኬንያና በሶማሊያ ድንበር አካባቢ ነው፡፡ እኔና ሌሎችም በቁጥጥር ሥር የዋሉት የውጭ ዜጎች ኢትዮጵያ በገባንበት ወቅት ፍርድ ቤት ቀርበናል፡፡ ምግብ ልብስ፣ መጠለያና የምንፈልጋቸውን ነገሮች ሁሉ አግኝተናል፡፡ የኢትዮጵያ የጸጥታ ኃይሎች ጥሩዎች ናቸው፡፡ እንደ ጓደኞቼ ነው የማያቸው፡፡" ብሏል፡፡<br>
<br>
አፕ ሳውንድ 4ኛ ተናጋሪ ሙኒር አዋድ መግቢያ 0፡09 "ጥሩ ነገር4 ነው ያለው፡፡ ጥሩ ሁኔታ እንዳለ ይሰማኛል፡፡ ጥሩ ምግብ ይቀርብልናል፡፡ ጥሩ እንክብካቤ እያደረጉልን ነው፡፡"<br>
<br>
ባለትዳር እንደሆነ የገለጸው ሙኒር አዋድ በኢትዮጵያ ቆይታው ምንም ዓይነት ችግር እንዳለጋጠው ተናግሯል፡፡<br>
<br>
በአሸባሪነት ተጠርጥረው በቁጥጥር ሥር ከዋሉትና በኢትዮጵያ ከሚገኙት የውጭ ዜጎች መካከል በዩክሬን ተወልዶ የሶሪያ ዜግነት እንዳለው የገለጸው ኦሳማ አብደልአዚዝ አል-ናሲፍ በደቡባዊ ኬንያ አካባቢ በቁጥጥር ሥር መዋሉንና ወደ ኢትዮጵያ እንደገባም ፍርድ ቤት መቅረቡን ገልጿል፡፡<br>
<br>
የጥርስ ሕክምና የሁለተኛ ዓመት ተማሪ እንደነበር የገለጸው ኦሳማ አብደልአዚዝ አል-ናሲፍ እንደተናገረው ምግብ፣ መጠለያና ሌሎችም መሠረታዊ ፍላጎቶች በወቅቱ እየቀረበለት ነው፡፡<br>
<br>
"በኢትዮጵያ ቆይታዬ ምንም ያጋጠመኝ ችግር የለም፡፡ ደስተኛም ነኝ፡፡ የኢትዮጵያን መንግሥት አመሰግናለሁ፡፡" ብሏል፡፡<br>
<br>
5ኛ ተናጋሪ ኦሳማ አብደልአዚዝ አል-ናሲፍ መግቢያ 0፡11 "ወንድሞቼና ጓደኞቼ የሆኑት የኢትዮጵያ ፖሊሶች ጥሩ ነገር እያደረጉልኝ ነው፡፡ ከኢትዮጵያ መንግሥት ጥሩ ምግብና ልብስ እየቀረበልን ነው፡፡ የኢትዮጵያ መንግሥትን በጣም አመሰግናለሁ፡፡" መውጫ 0፡24<br>
<br>
ሌላው በኬንያ ድንበር አካባቢ በቁጥጥር ሥር ከዋሉት መካከል የኡጋንዳ ዜግነት እንዳለው የገለጸው ሙሳ ዌጆሊ ኢብራሂም ኦጃምቦ በበኩሉ በኢትዮጵያ ቆይታው ፍርድ ቤት መቅረቡንና ምንም ያጋጠው ችግር እንደሌለ ጠቅሶ ተገቢው የሰብዓዊ መብት ጥበቃ እየተደረገለት መሆኑን ተናግሯል፡፡<br>
<br>
ሌላው የሳኡዲ አረቢያ ዜግነት እንዳለው የገለጸው ጀሚል አብዱ አሊ በበኩሉ ወደ ኢትዮጵያ በገባበት ወቅት የኢትዮጵያ የጸጥታኃይሎች አስፈላጊውን እንክብካቤ እንዳደረጉለትና ፍርድ ቤትም መቅረቡን ገልጿል፡፡ በኢትዮጵያ ቆይታው እስካሁን ምንም ዓይነት የሰብዓዊ መብት ጥሰት እንዳላጋጠመውም ገልጿል፡፡<br>
<br>
በአሸባሪነት ተጠርጥረው በቁጥጥር ሥር ከዋሉትና በኢትዮጵያ ከሚገኙት የውጭ ዜጎች መካከል የታንዛኒያ ዜግነት እንዳለው የገለጸው ሞሐመድ አብሽር ሣሊም በበኩሉ በቁጥጥር ሥር ውሎ ወደ ኢትዮጵያ በገባበት ወቅት ፍርድ ቤት መቅረቡን ተናግሯል፡፡<br>
<br>
በኢትዮጵያ ቆይታው አስፈላጊው እንክብካቤ እየተደረገለት እንደሆነና ምንም ዓይነት ችግር እንዳላጋጠውም ገልጿል፡፡]]></description>
            <link>http://www.ena.gov.et/AmharicNews/2007/Apr/10Apr07/21983.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">3841B8B8-E78C-11DB-BB94-000393197FB0-421-00000012EAFAAB7B-FFA</guid>
            <pubDate>Tue, 10 Apr 2007 14:02:04 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት የተወሰኑ ጋዜጠኞች እንዲከላከሉ ወሰነ..</title>
            <description><![CDATA[አዲስ አበባ ሚያዝያ 2/1999 ሕገመንግሥቱንና በሕገመንግሥቱ መሠረት የተቋቋመውን ሥርዓት በአመጽ ለማፍረስ በፈጸሙት የሙከራ ወንጀል ክስ በተመሠረተባቸው በእነ ኢንጂነር ኃይሉ ሻውል መዝገብ ከተከሰሱት የህትመት፣ የማስታወቂያ ድርጅቶችና የጋዜጣ አዘጋጆች መካከል የተወሰኑት እንዲከላከሉ የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ትናንት ብይን ሰጠ፡፡<br>
<br>
በአምስተኛው ክስ ደግሞ ኤርትራ በኢትዮጵያ ላይ የጦርነት ስጋት እየፈጠረች በነበረችበት ጊዜ የቅንጅት መሪዎች በሚያካሂዷቸው ውይይቶችና ይሰጧቸው በነበሩ መግለጫዎች መነሻነት ሕገወጥ አላማቸውን ለማሳካት የሀገር መከላከያ ንብረት የሆነ መኪና በማቃጠልና በመጉዳት ቅንጅቱን ይመሩ ከነበሩት 16 ተከሳሾች መካከል ኢንጂነር ኃይሉ ሻውልን ጨምሮ አስሩ እንዲከላከሉ ብይን ሰጥቷል፡፡<br>
<br>
ሁለተኛ ወንጀል ችሎት ሲሳይ የህትመትና የማስታወቂያ ድርጅት፣ ዘካሪያስ አሳታሚ፣ ሰርካለም አሳታሚ ድርጅት፣ የኢትኦጵ ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ አቶ አንዱዓለም አየለ፣ የአባይ ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ አቶ መስፍን ተስፋዬ እና የሳተናው ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ አቶ ዳዊት ፋሲል እንዲከላከሉ ብይን ሲሰጥ ጉዳያቸው በሌሉበት የታየው የምኒልክ ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ ዘላለም ገብሬ እና የነፃነት ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ አቶ አብይ ግዛው ላይ ደግሞ የጥፋተኝነት ውሳኔ ሰጥቷል፡፡<br>
<br>
በሁለተኛው ክስ በቅንጅት ላእላይ ምክር ቤት ይደረጉ በነበሩት ስብሰባዎች የምርጫ ቦርድ በሕገ መንግሥቱ በተሰጠው ስልጣን መሠረት ተግባሩን እንዳያከናውን የማሰናከል ድርጊት ፈጽመዋል ተብለው ክስ ktm\rtÆቸውÂ ጉዳያቸው ባሉበት የታየው 21 ተከሳሾች እንዲከላከሉ ጉዳዩ በሌለበት የታየው ብሩክ ከበደ ላይ ደግሞ የጥፋተኝነት ውሳኔ አስተላልፏል፡፡<br>
<br>
በሦስተኛው ክስ በቅንጅት ለአንድነት እና ለዴሞክራሲ በተሰኘ ድርጅት ስር ተሰባስበው በሕገመንግሥቱ በተቋቋሙ አካላት ላይ የኃይል ጥቃት ለመፈፀም ሕገ ወጥ ታጣቂዎችንና ሽፍታዎችን የማደራጀት ሥራ ማከናወናቸው በማስረጃ የተረጋገጠባቸው ኢንጂነር ኃይሉ ሻውል፣ አቶ ማሙሸት አማረ፣ አባይነህ ብርሃኑና ሻለቃ ጌታቸው መንግሥቴ እንዲከላከሉ ፍርድ ቤቱ ብይን ሰጥቷል፡፡<br>
<br>
በአንደኛው ክስ ተመስርቶባቸው የነበሩ 25 ጋዜጠኞች፣ የሕትመትና የማስታወቂያ ድርጅቶች ኃላፊዎችና ባለቤቶች ደግሞ መከላከል አያስፈልጋቸውም በማለት ፍርድ ቤቱ ብይን በመስጠት ከማረሚያ ቤት እንዲፈቱ ዋራንት እንዲጻፍ ትእዛዝ ሰጥቷል፡፡ እንዲሁም በሁለተኛው ክስ ተመስርቶባቸው የነበሩ 37 ሰዎችና ድርጅቶች ደግሞ መከላከል አያስፈልጋቸውም ሲል ፍርድ ቤቱ ብይን ሰጥቷል፡፡<br>
<br>
በአምስተኛው ክስ ደግሞ ሕገወጥ አላማቸውን ለማሳካት ኤርትራ በኢትዮጵያ ላይ የጦርነት ስጋት እየፈጠረች በነበረችበት ጊዜ የቅንጅት መሪዎች ከጥቅምት ወር 1997 ዓ.ም ጀምሮ በሚያካሂዷቸው ውይይቶችና ይሰጧቸው በነበሩ መግለጫዎች መነሻነት የሀገር መከላከያ ንብረት የሆነ መኪና በማቃጠልና በመጉ ዳት ቅንጅቱን ይመሩ ከነበሩት 16 ተከ ሳሾች መካከል ኢንጂነር ኃይሉ ሻውል፣ አቶ አባይነህ ብርሃኑ፣ ሻለቃ ጌታቸው መንግሥቴ፣ ኢንጂነር ግዛቸው ሽፈራው፣ አቶ ሙሉነህ ኢዮኤል፣ ዶክተር ብርሃኑ ነጋ፣ ዶክተር በፈቃዱ ደግፌ፣ ዶክተር ኃይሉ አርአያ፣ ዶክተር ያዕቆብ ኃይለ ማርያምና አቶ ስለሺ ጠና የተባሉት እንዲከላከሉ ፍርድ ቤቱ ብይን ሰጥቷል፡፡<br>
<br>
በአንደኛው ክስ የተመሰረተባቸው የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት -መኢአድ-ቅንጅት? የኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ አንድነት ፓርቲ-መድህን፣ የኢትዮጵያን ዴሞክራሲያዊ ሊግ እና ቀስተደመና ኢትዮጵያ የዴሞክራሲና የማኅበራዊ ፍትህ ንቅናቄ (ቀስተደመና(QNJT) የፖለቲካ ድርጅት የሚከሰሱት በሌላ አንቀፅ መሆኑን በመግለፅ አሁን በክሱ የተጠቀሰባቸው የሕግ አንቀፅ የሚከሰሱበት ባለመሆኑ መከላከል አያስፈልጋቸውም ሲል ችሎቱ ብይን ሰጥቷል፡፡<br>
<br>
ፍርድ ቤቱ በትናንት ውሎው ዓቃቤ ሕግ በተራ ቁጥር ስድስትና በተራ ቁጥር ሰባት ያቀረባቸውን ክሶች አይቶ ተከሳሾቹ መከላከል አያስፈልጋቸውም በማለት በአብላጫ ድምጽ ብይን ሰጥቷል፡፡<br>
<br>
በሃሳብ የተለየው አነስተኛው ድምጽ ደግሞ በአገር ክህደቱና በዘር ማጥፋት ወንጀሉ በተከሳሾች ላይ የተመሰከረባቸው በመሆኑ ሊከላከሉ ይገባል በማለት የሃሳብ ልዩነቱን አስቀምጧል፡፡<br>
<br>
በተመሰረተባቸው ክስ መልስ ሳይሰጡ የቆዩት ተከሳሾች ተከላከሉ የተባሉበት የሕግ አንቀጽ ከባድ በመሆኑ መከላከል ይፈልጉ እንደሆነ ሃሳባቸውን አስተካክለው እንዲመጡ ወይም በጽሕፈት ቤት በኩል እንዲያመለክቱ ትእዛዝ በመስጠት ለሚያዝያ 22 ቀን 1999 ፍርድ ቤቱ ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡<br>
<br>
 ጠበቃ አቁመው ይከራከሩ የነበሩት ተከሳሾችም የመከላከያ ማስረጃ ካላቸው በጽሕፈት ቤት በኩል እንዲያቀርቡና መጥሪያ ወስደው የመከላከያ ምስክሮቻቸውን አስቀርበው እንዲያሰሙ ፍርድ ቤቱ ትዕዛዝ ሰጥቷል፡፡ ዓቅቤ ሕግ በተራ ቁጥር አራት ቀርቦ የነበረውን ክስ ቀደም ሲል ማንሳቱ ይታወሳል፡፡]]></description>
            <link>http://www.waltainfo.com/AmNews/2007/Apr/10Apr07/27309.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">F598A4DD-E78B-11DB-BB94-000393197FB0-421-000000120D8FC7CC-FFA</guid>
            <pubDate>Tue, 10 Apr 2007 14:01:32 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>በጎንደር ከተማ መጪውን ሚሊኒየም በታላቅ ድምቀት ለማክበር የሚያስችል ምክርቤት ተቋቋመ...</title>
            <description><![CDATA[ጎንደር ሚያዝያ 2/1999/ዋኢማ/በጎንደር ከተማ መጪውን ሚሊኒየም በታላቅ ድምቀት ለማክበር የሚያስችል የሀገር ሽማግሌዎችንና የተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎችን ያካተተ ምክርቤት ተቋቋመ።<br>
<br>
በጎንደር ከተማ ሰሞኑን በተካሄደ የሚሊኒየም መሥራች ጉባኤ የተቋቋመው ምክርቤት የከተማዋ ታዋቂ የአገር ሸማግሌዎች የተለያዩ የመንግሥት መሥሪያ ቤት ሠራተኞችንና የኅብረተሰብ ክፍሎችን ያቀፈ ነው።<br>
<br>
በመሥራች ጉባኤው የተቋቋመው የሚሊኒየም ምክር ቤት በሥሩ 11 ሥራ አስፈፃሚ አባላት ያሏቸው ስድስት ንዑሳን ኮሚቴዎችአሉት።<br>
<br>
የሚሊኒየም ምከርቤቱ አባላት ባስተላለፉት መልክት በጎንደር ከተማ ሊሰራ የታቀደውን ሪፈራል ሆስፒታል ግንባታ ለማስጀመር፤ኤች አይቪ ኤድስን ለመከላከል፤ከተማዋን ማስዋብ፤ቅርሶችንና የተፈጥሮ ሀብቶችን<br>
<br>
ለመንከባከብ ኅብረተሰቡ የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣ አሳስበዋል።<br>
<br>
በሚሊኒየም ምክር ቤቱ መሥራች ጉባኤ የተገኙት የጎንደር ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ አቶ መጋቢያው ጣሰው ባደረጉት ንግግር፤ ከተማዋ በአገሪቱ ታሪክ የነገስታት መናገሻ በመሆን ያላትን ፈርጀ ብዙ ታሪክ በማስተዋወቅ ለመጪው ትውልድ ለማስረከብ የከተማዋ ነዋሪ በዓሉን ለማክበር መነሳሳት ይጠበቅበታል ብለዋል።<br>
<br>
ሚሊኒየሙን በማስመልከት በከተማዋ አንገረብ ግድብ አካባቢ ሊቋቋም ለታሰበው ፓርክ በዕለቱ በክብር እንግድነት የተገኙት የሰሜን ጎንደር ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ጌታቸው ጀምበርና የአማራ መልሶ መቋቋም ልማት ድርጅት /አመልድ/ዳይሬክተር አቶ ውለታው ሀይለማሪያም የመሰረት ድንጋይ አኑረዋል።<br>
<br>
የአማራ መልሶ መቋቋም ልማት ድርጅት /አመልድ/ዳይሬክተር አቶ ውለታው ኃይለማሪያም እንደተናገሩት፣ የከተማዋን የተፈጥሮ ሀብት ለመንከባከብ ለሚደረገው ጥረት አመልድ ከ3 ሚሊየን በላይ ልዩ ልዩ ችግኞችን ለማቅረብ ቃል ገብተዋል።<br>
<br>
በመሥራች የሚሊኒየም ምክር ቤቱ ጉባኤ በከተማዋ ሥራ አጥነትን ለመቀነስ ጉልህ አስተዋጽኦ ይኖራቸዋል ተብለው የታመነባቸው ከሚሊኒየሙ ጋር ተያይዘው ሊሰሩ የታቀዱ ዝርዝር ፕሮጀክቶች ቀርበው መጽደቃቸውን ዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል ዘግቧል።]]></description>
            <link>http://www.waltainfo.com/AmNews/2007/Apr/10Apr07/27278.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">E4E5CE93-E78B-11DB-BB94-000393197FB0-421-00000011D6189922-FFA</guid>
            <pubDate>Tue, 10 Apr 2007 14:01:58 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>ኢትዮጵያ የምዕተ ዓመቱን ግብ ለማሳካት ባስመዘገበችው እጅግ አበረታች ውጤት በመንግስታቱ ድርጅት ዓለም አቀፍ ስብሰባ ላይ ገለጻ እንድታደርግ ተመረጠች...</title>
            <description><![CDATA[አዲስ አበባ ሚያዚያ 2/1999/ዋኢማ/ ኢትዮጵያ የምዕተ ዓመቱን ግብ ለማሳካት ባደረገችው ጥረት እጅግ አበረታች ውጤት በማስመዝገቧ በመጪው ሐምሌ ጀኔቫ ላይ በከፍተኛ ሚኒስትሮች ደረጃ በሚካሄደው የተባበሩት መንግስታት የኢኮኖሚና ማህበራዊ ምክር ቤት ዓመታዊ ስብሰባ ላይ ውጤታማነቷን በተመለከተ ገለፃ እንድታደርግ መመረጧ ተገለፀ። ጋናም የዚሁ ዕድል ተጋሪ መሆኗን ተገልጿል።<br>
<br>
<br>
የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን የምስራቅ አፍሪካ ጽህፈት ቤት ዳይሬክተር ፓትሪክ ቡጌምቤ ለዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል እንደገለፁት፤ ኢትዮጵያ የምዕተ ዓመቱን ግቦች ለማሳካት ውጤታማ ስራ በማከናወኗ አገሪቱ ያስመዘገበቻቸውን ውጤቶች በተመለከተ በመንግስታቱ ድርጅት የኢኮኖሚና ማህበራዊ ምክር ቤት ስብሰባ ላይ ገለፃ እንድታደርግ ተጠይቃለች።<br>
<br>
[የዳይሬክተሩ ድምፅ]<br>
<br>
" ኢትዮጵያ የምዕተ ዓመቱን ግቦች ላማሳካት እጅግ አመረቂ ተግባሮችን አከናውናለች። ስለዚህም አገሪቱ ያስመዘገበቻቸውን ውጤቶች በተመለከተ ጄኔቫ ላይ በከፍተኛ ሚኒስትሮች ደረጃ በሚካሄደው ዓመታዊ የተባበሩት መንግስታት የኢኮኖሚና ማህበራዊ ምክር ቤት ላይ ተገኝታ ገለጻ እንድታደርግ ተጠይቃለች። እኛም አገሪቱ በስብሰባው ላይ ተግኝታ ገለጻ ለማድረግ ለምታደርገው ዝግጅት ዕገዛ እናደርጋለን።"<br>
<br>
<br>
በዚህም ጽህፈት ቤቱ ኢትዮጵያ በገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር አማካኝነት በስብሰባው ለመገኘት የምታደርገውን ዝግጅት በመደገፍ ላይ እንደሚገኝ ገልጸው፤ ይህም አገሪቱ የምዕተ ዓመቱን ግቦች በማሳካት ረገድ ያስመዘገበችው ስኬት ለዓለም ህብረተሰብ ማሳየት እንደሚያስችላት አመልክተዋል።<br>
<br>
<br>
ጋናም ባከናወነችው ውጤታማ ስራና ባስመዘገበችው አበረታች ውጤት ከኢትዮጵያ እኩል በስብሰባው ላይ ገለፃ እንድታደርግ መመረጧን ዳይሬክተሩ ተናግረዋል።<br>
<br>
ይህ በእንዲህ እንዳለ የዓለም ባንክና ሌሎች መሰል ተቋማት በኢትዮጵያ የታየውን የዋጋ ግሽበት በተመለከተ ከሚያካሂዳቸው ጥናቶች በተጨማሪ የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን የምስራቅ አፍሪካ ጽህፈት ቤት በዋጋ ግሽበቱ ላይ ጥናት እንዲያካሂድ የኢትዮጵያ መንግስት መጠየቁን ተናግረዋል።<br>
<br>
የኢትዮጵያ መንግስት ጥያቄውን ያቀረበው በአሁኑ ወቅት በሀገሪቱ የሚታየውን የዋጋ ግሽበት በተመለከተ እንደ አፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ባሉ ገለልተኛ ተቋማት ቢረጋገጥ የተሻለ ነው ብሎ ስለሚያምን እንደሆነም አስረድተዋል።<br>
<br>
የአፍሪካ አኮኖሚክ ኮሚሽን የምስራቅ አፍሪካ ክፍለ አህጉራዊ ዕህፈት ቤት ከግብርናና ገጠር ልማት ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ኢትዮጵያ የምታካሂዳቸውን የገጠር ልማት ስራዎች ለማገዝ እንደሚሰራም ዳይሬክተሩ መናገራቸውን ዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል ዘግቧል።]]></description>
            <link>http://www.waltainfo.com/AmNews/2007/Apr/10Apr07/27306.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">7EFD6A3A-E788-11DB-BB94-000393197FB0-421-000000068CA25D2B-FFA</guid>
            <pubDate>Tue, 10 Apr 2007 14:01:53 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>ሻዕቢያ በኩናማ ብሄረሰብ አባላት ላይ የሚያደርገውን አፈና አጠናክሮ መቀጠሉን ተገለጸ...</title>
            <description><![CDATA[መቀሌ ሚያዝያ 2/1999/ዋኢማ/ የሻዕቢያ መንግስት በኤርትራውያን ላይ በተለይም በጋሽ ባርካ አካባቢ በሚገኙ የኩናማ ብሄረሰብ አባላት ላይ የሚያደርገውን አፈና አጠናክሮ መቀጠሉን የኤርትራ ኩናማ ዴሞክራሲያዊ ነጻነት እንቅስቃሴ/ደምሐኩኤ/ ገለጸ።<br>
<br>
የኤርትራ ኩናማ ዴሞክራሲያዊ ነጻነት እንቅስቃሴ ዛሬ ለዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል እንደገለጸው፤ የሻዕቢያ መንግሥት ወደ ወታደራዊ ማሰልጠኛ ተቋማት በሚወስዳቸው ኤርትራውያን ተቃውሞ እየበረታበት ባለበት በአሁኑ ወቅት በተለይም ካለፈው ወር ጀምሮ በኩናማ ብሄረሰብ አበላት ላይ መጠነ ሰፊ አፈና እያካሄደ ይገኛል።<br>
<br>
የሻዕቢያ መንግሥት እየተከተለ ባለው የአፈና ስልት አፋኝ አባላቱን በተራሮች፣ በኮረብታዎችና በየጢሻው በማሰማራት ለእርሻ ስራ የተሰማሩ የኩናማ ወጣቶችን አስገድዶ መውሰድ ሲሆን፤ ወጣቶቹ እንዳያመልጡ አሊያም ተቃውሞአቸውን እንዳያሰሙ ጫማቸውን አስወልቆ እጃቸውን በገመድ አስሮ ረጅም መንገድ እንዲጓዙ በማድረግ እንያሰቃያቸው እንደሚገኝ አመልክተዋል።<br>
<br>
እንዲህም ሆኖ ለማምለጥ የሚሞክሩትን ያለምንም ርህራሄ በጥይት እንዲገደሉ በማዘዝ በየሜዳው ወድቀው እንዲቀሩ እያደረገ መሆኑን ድርጅቱ አጋልጧል።<br>
<br>
ሻዕቢያ በእጁ የወደቁት ኤርትራውያንን በሞቃታማነቱ ወደ ታወቀው ዊዓ ማሰልጠኛ ማዕከል እንደሚወስዳቸውና በኪሳቸው የተገኘ ገንዘብና ንብረትም እንደሚቀማቸው ድርጅቱ አመልክቷል።<br>
<br>
ሻዕቢያ ወደ ዊዓ ከወሰዳቸው በርካታ የኩናማና የሌሎች ብሄር ተወላጆች በተለይም ታዳጊ ወጣቶች ሙቀቱን መቋቋም አቅቷቸው ለከባድ የሥነ ልቦና ጭንቀት በመጋለጣቸው ወደ ሳዋ ማሳልጠኛ ተቋም እያዛወራቸው እንደሚገኝም አስታውቋል።<br>
<br>
አፋኙ የሻዕቢያ ወታደራዊ ኃይል በኩናማ ሚሊሻዎች ተቋውሞ መደናገጡን ድርጅቱ ጠቅሶ፤ የኩናማ ሚሊሻዎች በአካባቢያቸው ወደ ሚገኘው ከርካሻና በረንቱ መስተዳድሮች መሳሪያዎቻቸውን እንዲያስረክቡ እያደረገ መሆኑንም ገልጿል።<br>
<br>
የሻዕቢያ መንግሥት ተስፋ እየቆረጠ በመምጣቱ በቅርቡ በበረንቱ ከተማ ባደረገው ስብሰባ የኤርትራ ነጻነት የመጣው የሚያጠቡ እናቶች ጭምር ባደረጉት ተጋድሎ ስለሆነ ከሁለት እስከ ሦስት የወለዱ እናቶች መሳሪያ እንዲታጠቁ አዲስ መመሪያ ማውጣቱን ድርጅቱ ገልጿል።<br>
<br>
በስብሰባው የተገኙ እናቶችም በሻዕቢያ መንግሥት የወጣውን መመሪያ መቃወማቸውንና በግዳጅ ያዘመተናል የሚል ሥጋት ላይ መውደቃቸውን ድርጅቱ አመልክቷል።]]></description>
            <link>http://www.waltainfo.com/AmNews/2007/Apr/10Apr07/27275.htm</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">51DB0074-E788-11DB-BB94-000393197FB0-421-00000005F6B78AAC-FFA</guid>
            <pubDate>Tue, 10 Apr 2007 14:01:48 -0400</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>የኤርትራ ሄሊኮፕተር ሣዑዲ አረቢያ አረፈ አብራሪውና ረዳቱ በሣዑዲ አረቢያ የፖለቲካ ጥገኝነት ጠየቁ</title>
            <description>የኤርትራ ሄሊኮፕተር ሣዑዲ አረቢያ አረፈ አብራሪውና ረዳቱ በሣዑዲ አረቢያ የፖለቲካ ጥገኝነት ጠየቁ&lt;br&gt;
አዲስ አበባ, ታህሳስ 14 ቀን 1999 (አዲስ አበባ) - የኤርትራ ሄሊኮፕተር በትናንትናው ዕለት ሣዑዲ አረቢያ ማረፉንና የሄሊኮፕተሩ አብራሪና ረዳቱ በሣዑዲ አረቢያ የፖለቲካ ጥገኝነት መጠየቃቸውን የአገሪቱ መንግሥት የመገናኛ ብዙሃን አስታወቀ፡፡&lt;br&gt;
የሣዑዲ አረቢያ የመንግሥት መገናኛ ብዙሃን የአገሪቱን የመከላከያ ሚኒስቴር ባለሥልጣን በመጥቀስ ባሰራጨው ዘገባ ሩሲያ ሰራሽ የሆነው ሄሊኮፕተር ወደ ሣዑዲ አረቢያ የአየር ክልል በመግባት ከአገሪቱ የአውሮፕላን ጣቢያ ጋር አስቸኳይ ግንኙነት በመፍጠር በአገሪቱ ደቡባዊ ምዕራብ አርፏል፡፡&lt;br&gt;&lt;br&gt;
የሣዑዲ አረቢያ የመከላከያ ባለሥልጣን የኤርትራ ሄሊኮፕተር አብራሪና ረዳቱ ሄሊኮፕተሩን በሣዑዲ አረቢያ ደቡባዊ ምዕራብ ካሳረፉ በኋላ በአገሪቱ የፖለቲካ ጥገኝነት መጠየቃቸውን አስታውቀዋል፡፡&lt;br&gt;&lt;br&gt;
ሮይተርስ የሣዑዲ አረቢያን የመንግሥት መገናኛ ብዙሃን በመጥቀስ ባሰራጨው ዘገባ የአገሪቱ የመከላከያ ባለሥልጣን በሁኔታው ላይ ምርመራ እንደተጀመረ ይፋ ማድረጋቸውን ገልጿል፡፡</description>
            <link>http://www.amhariczena.com/index.php?ind=news&amp;op=news_show_category&amp;idc=2</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">31544F7F-92EF-11DB-9403-000393197FB0-456-0000021CDF83EA48-FFA</guid>
            <pubDate>Sat, 23 Dec 2006 21:36:36 -0500</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>የፌዴራል ፖሊስ አንድ እንግሊዛዊ 8 ኪሎ የሚመዝን ካናቢስ የተባለውን አደንዛዥ እጽ ይዞ ሊወጣ ሲል መያዙን አስታወቀ</title>
            <description><![CDATA[የፌዴራል ፖሊስ አንድ እንግሊዛዊ 8 ኪሎ የሚመዝን ካናቢስ የተባለውን አደንዛዥ እጽ ይዞ ሊወጣ ሲል መያዙን አስታወቀ<br>
አዲስ አበባ, ታህሳስ 14 ቀን 1999 (አዲስ አበባ) -<br>
የፌደራል ፖሊስ የአደገኛ እጽዋት መቆጣጠሪያ ክፍል አንድ እንግሊዛዊ 8 ኪሎ ግራም የሚመዝን ''ካናቢስ'' የተባለውን አደንዛዥ እጽ ይዞ ከአገር ሊወጣ ሲል በቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ መያዙን አስታወቀ፡፡<br>
<br>
ተጠርጣሪው ወንጀለኛ በባህላዊ ዘዴ በተሰሩ የራስጌ መብራቶች ውስጥ አደንዛዥ እጹን በማስገባት በእንግሊዝ አየር መንገድ ከአገር ሊወጣ ሲል በተደረገ ፍተሻ መያዙን በፌዴራል ፖሊስ የአደገኛ እጽዋት መቆጣጠሪያ አገልግሎት ኃላፊ ዋና ኢንስፔክተር ደጀኔ በቀለ ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ገልጸዋል፡፡<br>
<br>
በአራቱ የባህላዊ ራስጌ መብራቶች ውስጥ በእያንዳንዳቸው 2 ኪሎ ግራም የሚመዝነውን የአደገኛ እጽዋት ይዞ የተገኘው እንግሊዛዊ ሰዎች እንዲያደርስ እንደሰጡት የገለጸ ቢሆንም ጉዳዩ በቀጣይ ምርመራዎች እንደሚጣራ ዋና ኢንስፔክተሩ አስታውቀዋል፡፡<br>
<br>
ወንጀሉን ለመፈጸም የተሞከረው በባህላዊ መልክ በተሰሩት የራስጌ መብራቶች ውስጥ አደንዛዝ እጾችን በማስገባትና በውስጣቸውም የኤሌክትሪክ ኃይል የሚያልፈበት ገመድ በማስገባት በተለምዶ የኤሌክትሪክ ኃይል ሲያልፍባቸው የሚሰሩ መሳሪያዎች በፍተሻ ስለሚያልፉ ያን አጋጣሚ በመጠቀም አደንዛዥ እጾች ለማሳለፍ የተደረገ ሙከራ እንደሆነ ኃላፊው አስረድተዋል፡፡<br>
<br>
ሆኖም እቃዎቹ ሲመለከቷቸውና ያላቸው ክብደት ተመጣጣኝ ባለመሆኑ ባሰደረው ጥርጣሬ ሌሎች ዘመናዊ የፍተሻ መሳሪያዎችን በመጠቀም በውስጣቸው የታጨቀውን አደገኛ እጽ ለመያዝ እንደተቻለም ኃላፊው አብረራርተዋል፡፡<br>
<br>
ተጠርጣሪው እነዚህን እጾች ያመጣቸው ከሻሸመኔ ከተማ መሆኑን የገለጸ ሲሆን ወደ እንግሊዝ አገር ይሄድ እንደነበርም ኃላፊው ገልጸዋል፡፡<br>
<br>
ከዚህ ቀደም ዓለም አቀፍ የአደገኛ እጽ አዘዋዋሪዎች አደገኛ እጾችን ከአገር አገር ሲያዘዋውሩ በቦሌ የዓለም አቀፍ አውሮፕላን ጣቢያ መያዛቸውን ያስታወሱት ዋና ኢንስፔክተሩ የመደበቂያ ዘዴዎቻቸው የተለያዩና የረቀቁ ጭምር መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡<br>
<br>
የኢትዮጵያ የፌዴራል አደገኛ እጽዋት መቆጣጠሪያ ክፍል ከሌሎች ድጋፍ ሰጪ አገራት ጋር በመተባበር የአባሎቹን አቅም የማጎልበት ተግባር ከጊዜ ወደ ጊዜ እያሳደገ መምጣቱንና ወደፊትም ይህን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ዋና ኢንስፔክተሩ አስታውቀዋል፡፡<br>
<br>
አደገኛ እጾች ሌሎች የአስገድዶ መድፈር፣ ስርቆት፣ ዘረፋና ተመሳሳይ ወንጀሎች እንዲፈጸሙ የሚያበረታቱ በመሆናቸው ፖሊስ በሚያደርገው የመከላከልና የመቆጣጠር ተግባር ላይ ህብረተሰቡ የበኩሉን አስተዋጽኦ አንዲያደርግ ኃላፊው ጥሪ አቅርበዋል፡፡<br>
<br>
ተጠርጣሪው ስለጉዳዩ ማብራሪያ ለመስጠት ተጠይቆ ፈቃደኛ ባይሆንም በተደጋጋሚ ግን ''ደደብ በመሆኔ ወደ እስር ቤት እሄዳለሁ፤ ደደቡ እኔ ነኝ፡፡ ስለዚህ ወደ ወህኒ መውረድ ያለብኝ እኔ ነኝ፡፡ '' ብሏል፡፡]]></description>
            <link>http://www.amhariczena.com/index.php?ind=news&amp;op=news_show_category&amp;idc=2</link>
            <author>webmaster@ectv.org</author>
            <guid isPermaLink="false">698BBC9A-92EE-11DB-9403-000393197FB0-456-0000021A47EB33E9-FFA</guid>
            <pubDate>Sat, 23 Dec 2006 21:31:55 -0500</pubDate>
        </item>

        <item>
            <title>ኢትዮጵያ የቡና አብቃይ አካባቢዎችን ሥም በንግድ ምልክት ማስመዝገቧ የሚበረታታ ነው ወርልድ ዋይድ ሰስቴነብል ኮፊ ፈንድ የተባለው ዓለም ዓቀፍ ተቋም ድጋፍ እንደሚሰጥ ገለጸ</title>
            <description><![CDATA[ኢትዮጵያ የቡና አብቃይ አካባቢዎችን ሥም በንግድ ምልክት ማስመዝገቧ የሚበረታታ ነው ወርልድ ዋይድ ሰስቴነብል ኮፊ ፈንድ የተባለው ዓለም ዓቀፍ ተቋም ድጋፍ እንደሚሰጥ ገለጸ<br>
አዲስ አበባ, ታህሳስ 14 ቀን 1999 (አዲስ አበባ) -<br>
ኢትዮጵያ የቡና አብቃይ አካባቢዎችን ሥም በንግድ ምልክት ማስመዝገቧ የሚበረታታ በመሆኑ ድጋፉን እንደሚሰጥ "ወርልድ ዋይድ ሰስቴነብል ኮፊ ፈንድ" የተባለው ዓለም ዓቀፍ ተቋም አስታወቀ፡፡<br>
<br>
የኢትዮጵያ አዕምሯዊ ጽህፈት ቤት ፈንዱ የጻፈለትን የማበረታቻ ደብዳቤ ጠቅሶ ለኢዜአ እንደገለጸው የኢትዮጵያ የጀመረችው የቡና አብቃይ አካባቢ ሥያሜዎችን በንግድ ምልክት ለማስመዝገብ የጀመረችውን ጥረት ለማገዝ አስፈላጊውን ድጋፍ ይሰጣል፡፡<br>
<br>
የኢትዮጵያ እርምጃ ቡና አምራች ለሆኑ ታዳጊ አገራት አርአያ መሆኑንና ሌሎች አገሮችም ይህንኑ መንገድ ሊከተሉ እንደሚገባ ፈንዱ ማሳሰቡን በጽህፈት ቤቱ የሕግ፣ የፖሊሲና የፕላን ዳይሬክተር አቶ ወንድወሰን በለጠ አስታውቀዋል፡፡<br>
<br>
የኢትዮጵያን የቡና አብቃይ አካባቢ ሥያሜዎችን በንግድ ምልክት የማስመዝገብ ዓለም አቀፍ ጥረት እስካሁን ኦክስፋም አሜሪካ በከፍተኛ ደረጃ እየደገፈው እንደሚገኝ ጠቁመው "ወርልድ ዋይድ ሰስቴነብል ኮፊ ፈንድ" ተሰሚነት ያለው ዓለም አቀፍ ድርጅት በመሆኑ ተጨማሪ ዓለም አቀፍ ኃይል እንደሚሆን ዳይሬክተሩ ተናግረዋል፡፡<br>
<br>
ይህም "ስታርባክስ" የተባለው ድርጅት የኢትዮጵያን ጥረት በአሳሳች መረጃዎች ከግብ እንዳይደርስ እንቅፋት እየፈጠረ መሆኑን ጠቅሰው የነዚህ ወገኖች የተባበረ ድምጽና ሌሎችም የቡና ኩባንያዎች የኢትዮጵያን አቋም እንደተቀበሉት ሁሉ "ስታርባክስ" ወደ ትክክለኛው አቋሙ ሊመልሰው ይችላል ብለዋል፡፡<br>
<br>
እአአ 2004 ቡናውን ሽርክና ስንድራይድ ሲዳሞ በሚል "ስታርባክስ" በአሳሳች መረጃዎች በአሜሪካ የፓተንትና ንግድ ምልክት ጽህፈት ቤት የንግድ ፍቃድ አውጥቶበታል፡፡<br>
<br>
ድርጅቱ ይህንን የባለቤትነት መብትና ምዝገባ እንዲያነሳና የሲዳሞን ቡና በንግድ ምልክትነት ኢትዮጵያ እንዳታስመዘግብ በተለያዩ ወቅቶች ቢጠየቅም ድርጅቱ በቀጥታና በተዘዋዋሪ እንቅፋት እየፈጠረ ይገኛል፡፡<br>
<br>
ኢትዮጵያ እአአ ከ1929 ጀምሮ የሲዳሞን ቡና ለአሜሪካ ስታቀርብ ቆይታለች፡፡]]></description>
            <link>http://www.amhariczena.com/index.php?ind=news&amp;op=news_show_category&